Friday, January 27, 2023

አደባባይ እየውጣ ያለው የብልጽግና ስውር እጅ

  •  በቅዱስ ሲኖዶስ ተውግዞ የተለየው ቡድን ዛሬ ከኦሮሚያ ክልል ደህንነት ቢሮ ሃላፊ ጋር በዝግ ውይይት እያደረጉ ይገኛል። የውይይቱን ይዘት እንደደረሰን ይዘን እንመጣለን።
  •  “መቀመጫችሁን አዲስ አበባ ማድረግ አለባችሁ እኛም ከጎናችሁ ነን።” ሺመልስ አብዲሳ
  •  አዲስ አበባና በአዲስ አበባ ያሉ አድባራትና ገዳማትን በቀጣይ የግጭት ቀጠና ለማደርግ እየተሰራ ይገኛል።

 በቅዱስ ሲኖዶስ ተውግዞ የተለየው ቡድን መቀመጫ መንበራቸውን በወለጋ ለማድረግ አስቀድመው ባቀዱት መሰረት እየተንቀሳቀሱ የነበረ ቢሆንም የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ከተላለፈ በኋላ በኦሮሚያው ፕሬዝዳንት በተሰጠ መመሪያ በአዲስ አበባ እንዲያደርጉ ታዘዋል። ይህም በቀጣይ የቤተ ክርስቲያንን ሃብት መካፈል አለብን በሚል ሰበብ አዲስ አበባንና በአዲስ አበባ ያሉ አድባራትና ገዳማትን የግጭት ቀጠና ለማድረግ እየሰሩ ይገኛል።

ዘግይቶ በደረሰን መረጃ ሕገወጥ ሿሚዎቹና ተሿሚዎቹ ከሹመቱ በኋላ ወደ አዲስ አበባ እንደደረሱ ለደህንነታቸው አመች ነው በማለት ከኋላ ሁኖ በሚዘውራቸው የብልጽግና መንግስት በተዘጋጀላቸው በኦሮሚያ ጠቅላይ ፖሊስ መምሪያ በሚገኝ ማረፊያ አስቀምጧቸው እንደነበር ታውቋል። በኋላ ላይ ለምን ወደ ሆቴል እንዲዛወሩ እንደተደረገ የታወቀ ነገር የለም።




No comments:

Post a Comment

በሲሞን መንገድ ላይ ተገኙት “አባ” ወ/ኢየሱስ ኢፋ (ፍቅሩ ኢፋ) - ክፍል ሁለት

  እኚህ ሰው የእግዚአብሔርን ጥሪ ተቀብለው መንፈሳዊ ትምህርታቸውን መጀመራቸው አያጠራጥርም። በዚህም የሕይወት ምርጫቸውንም ቅዱስ ጳውሎስ “እንደኔ ብትሆኑ እወዳለኹ” ያለውን ተከትለው በሙሉ ጊዜያቸው እግዚአብሔርን እያመሠ...