Thursday, January 26, 2023

የሌባ በሩ ጓሮ፣ ቀኑ ሌሊት

የብልጽግና መንግሥት ከበር ይልቅ በጓሮ በኩል ለመግባት በስመ ጵጵስና የመጡትን የሹመት ሌቦችን ለማደራደር ሌሊቱን ቀን እያደረገ ቤተ ክህነቱን በምሽት መውረር ተያይዞታል። ትናንት ጥር 17 ቀን 2015 ዓ.ም ምሽትም በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ቤት በመግባት የማግባባትና የማስፈራራት ሥራ ሲሠራ አምሽቷል። ሹመኞቹ በጓሮ ለመግባት የሚያደርጉትን የሌብነት ሩጫ ጨለማን ተገን ያደረጉ የመንግሥት ጀሌዎች የማግባቢያ መሰርሰሪያ ይዘው መግቢያ ቀዳዳ ሲፈልጉ በማደር ላይ ናቸው። ማስፈራሪያው በብፁዓን ሊቃ ጳጳሳት ላይ ብቻ ሳይወሰን አባ ገብረ ሥላሴን (አባ ሕጻን) መረጃ ለምን አወጡ በሚል ከፍተኛ ማዋከብ እያደረሰባቸው ይገኛል።





No comments:

Post a Comment

በሲሞን መንገድ ላይ ተገኙት “አባ” ወ/ኢየሱስ ኢፋ (ፍቅሩ ኢፋ) - ክፍል ሁለት

  እኚህ ሰው የእግዚአብሔርን ጥሪ ተቀብለው መንፈሳዊ ትምህርታቸውን መጀመራቸው አያጠራጥርም። በዚህም የሕይወት ምርጫቸውንም ቅዱስ ጳውሎስ “እንደኔ ብትሆኑ እወዳለኹ” ያለውን ተከትለው በሙሉ ጊዜያቸው እግዚአብሔርን እያመሠ...