Tuesday, January 24, 2023

ሰበር መረጃ


የመፈንቅለ ሲኖዶሱ መሪ መንግሥት ራሱ መሆኑን ገለጠ።

ሦስቱን ሊቃነ ጳጳሳት እጅ አድርጎ ሕገ ወጥ ሲመተ ጵጵስና ያሰጠው እና መፈንቅለ ሲኖዶስ ለማድረግ በመጣር ላይ የሚገኘው የብልጽግና መንግሥት የቤተ ክህነቱን ጥበቃ ፖሊሶች አንሥቷል።
በአሁኑ ሰዓት ደግሞ ሕገወጥ ሲመተ ጵጵስና ሲሰጡ የነበሩት ሦስቱ ሊቃነ ጳጳሳት በነገው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ላይ እንዲገኙ ለማስገደድ ደኅንነቶቹን አሠማርቷል። ደኅንነቶቹም ወደ ቅዱስ ፓትርያርኩ መኖሪያ ገብተው ይህን እንዲያደርጉ ትእዛዝ ቢያስተላልፉም ቅዱስ አባታችን በሕይወት እያለሁ ሊፈጸም አይችልም ብለው ቁርጥ አቋማቸውን አሳውቀዋቸዋል።
በዚህ ሰዓት ቤተ ክህነቱ ዙሪያውን በፌደራል ፖሊስ ተወርሯል። ይህም የተውኔቱ ደራሲና ከያኒ ራሱ መንግሥት መሆኑን የሚረጋገጥ ሁነት ነው።



No comments:

Post a Comment

በሲሞን መንገድ ላይ ተገኙት “አባ” ወ/ኢየሱስ ኢፋ (ፍቅሩ ኢፋ) - ክፍል ሁለት

  እኚህ ሰው የእግዚአብሔርን ጥሪ ተቀብለው መንፈሳዊ ትምህርታቸውን መጀመራቸው አያጠራጥርም። በዚህም የሕይወት ምርጫቸውንም ቅዱስ ጳውሎስ “እንደኔ ብትሆኑ እወዳለኹ” ያለውን ተከትለው በሙሉ ጊዜያቸው እግዚአብሔርን እያመሠ...