Monday, February 20, 2023

በሲሞን መንገድ ላይ ተገኙት “አባ” ወ/ኢየሱስ ኢፋ (ፍቅሩ ኢፋ) - ክፍል ሁለት


 

እኚህ ሰው የእግዚአብሔርን ጥሪ ተቀብለው መንፈሳዊ ትምህርታቸውን መጀመራቸው አያጠራጥርም። በዚህም የሕይወት ምርጫቸውንም ቅዱስ ጳውሎስ “እንደኔ ብትሆኑ እወዳለኹ” ያለውን ተከትለው በሙሉ ጊዜያቸው እግዚአብሔርን እያመሠገኑ ለመኖር ወስነው መንኩሰዋል። ግን ለዓለም አልሞቱም። ከክርስቶስ ፍቅር ይልቅ በዘራቸው ፍቅር ተለከፉ፣ከትህትና ይልቅ ትዕቢትን ገንዘብ አደረጉ። እራስን ዝቅ በማድረግ ከሚገኝ አምላካዊ ጸጋ ይልቅ በሰይጣን መንገድ ሄደው መከበርን ሻቱ፣አቦ አቦ መባል ናፈቃቸው። ስለዚህም በእነ ዋስይሁን አመኑና በገረመው አፈወርቅ ፖለቲካ ተጠለፉ። በአፋን ኦሮሞ እያገለገሉ አይናቸውን በጨው አጥበው “የኦሮሞ ሕዝብ በቋንቋው አይገለገልም።” ብለው ዋሹ። እውነታው ግን የሌላ ብሔር ተወላጅ የሆኑ አገልጋዮችን ማየት አለመፈለጋቸው እንደሆነ አብረዋቸው የኖሩ ሰዎች ጠንቅቀው የሚያውቁላቸው ጾራቸው ነው። 

 እንኳንስና እስከ መመንኮስ የደረሰ አገልጋይ ካህን፤ የትኛውም ኦርቶዶክሳዊ ምዕመን የሰው ልጆችን ልዩነት አክብሮ በሰውነታቸው የሃይማኖት፣የብሔር፣የሀብት፣የዕውቀት ወዘተ ልዩነት ሳያደርግ “ባልንጀራህን እንደራስህ አድርገህ ውደድ” ያለውን የጌታ ቃል እንዲፈጽም ግድ የሚለው ሃይማኖታዊ ህሊና ገንዘብ ያደረገ ነው። እኚህ ሰው ግን በጥላቻ የተሞሉ፣ነፍሰ ገዳዮችን በሀሳብ፣በገንዘብ እና በቁሳቁስ የሚደግፉ፣የኦሮሞ መንግስት ተሹሟል። አሁን ጊዜው የእኛ ነው በማለት ተስፋቸውን ከእግዚአብሔር አንስተው ምድራዊ መንግስትን የተደገፉ አሳዛኝ ሰው ናቸው።

የቀድሞው አባ ወ/ኢየሱስ ኢፋ እጅግ ሲበዛ ክብርን የሚፈልጉ የሁሉ አባት ከመሆን ይልቅ የአንድ ብሔር አባት መሆንና መባል የሚፈልጉ፣እጅግ ሲበዛ እልከኛ፣በድሎ ይቅርታ መጠየቅንም ሆነ ተበድሎ ይቅር ማለትን እንደውርደት የሚቆጥሩ ቅዱስ ጳውሎስ ፡ምናልባት ስለ እናንተ በከንቱ ደክመን ይሆናል።” ብሎ እንደተናገረው በከንቱ የተደከመባቸው ሰው ናቸው። ካላቸው የፖለቲካ አመለካከት የተነሳም በገረመው አፈወርቅ መልማይነት የዋስይሁን አመኑ የፖለቲካ ካድሬ ለመሆን የበቁ የኦሮሞ ነጻውጪ ታጋይ መነኩሴ ናቸው።

እኚህ ሰው ቀሚስ አጥልቀው፣ቆብ ደፍተው፣ጺማቸውን አንዠርገው ሲታዩ ለተመልካች የሃይማኖት አባት ይምሰሉ እንጂ ፈጽሞ ኦርቶዶክሳዊነት ያልገባቸው፣እንዲገባቸውም የማይፈልጉ ሲበዛ በራስ አምልኮ የተጠመዱ እና በድፍረት ሐጢያት ለመስራት ወደኋላ የማይሉ ግብዝ ሰው ናቸው። እውነት ለመናገር እንደነዚህ ያሉ አባቶች/ሙሉ ጊዜያቸውን ሰጥተው ቤተክርስቲያንን ለማገልገል የወሰኑ፣የአብነት ትምህርት በመጠኑም ቢሆን የቀጸሉ/ ሲገኙ እንደ አንድ ልጅ በስስት የሚታዩ የዋሁን የምዕራብ ወለጋ ምዕመናንን በተኩላ ከመነጠቅ የሚያድኑ እውነተኛ እረኞች ይሆናሉ ብሎ ተስፋ ያልጣለባቸው በእነሱም ያልተደሰተ ሃይማኖት ወዳድ ምዕመን እና የቤተክርስቲያን አባት አልነበረም።

ሆኖም ግን እነሱ ፖለቲከኞች በፈጠሩት የጨቋኝ ተጨቋኝ ትርክት አዕምሯቸው የታጠበ ለእውነት ቆሞ ጽድቅን ከመስራት ይልቅ በጎጥ ፖለቲካ ውስጥ ተዘፍቀው እግዚአብሔር የሰጣቸውን ፀጋ ተነጥዋል። ከክብርም ተዋርደዋል። እውነት ለመናገር እነኚህ ሰዎች ምንም የሃይማኖት ጥብቅና የሌላቸው፣እንቆምለታለን የሚሉትን የኦሮሞ ሕዝብ ለማገልገል ዕውቀቱም ፍላጎቱም የሌለቻው ናቸው። ለመንግስትም ሆነ ለእግዚአብሔር ለመታዘዝ ልባቸውን ያከበዱ እልከኞች ናቸው። መንግስትን ያስቀደምኩት በእነሱ እምነት አሁን ላይ ሁሉን አድራጊና ፈጣሪ ምድራዊ መንግስታቸው እንጂ የሰማይ አምላክ አይደለምና ነው።

ሰሞኑን “አይዟችሁ ከጎናችሁ ነኝ አንዳች አትፍሩ።” በማለት የልብ ልብ ሲሰጣቸው የከረመው መንግስት የሾሟቸው ጳጳሳት ይቅርታ ጠይቀው እንዲመለሱ ሲያደርግ፣ጓደኛቸው የቀድሞው አባ ገ/ማርያም “የበሬ ወለደ ተረት” ነው ብለው “መንግስትን ውሸታም ነህ” ሲሉት አላፈሩም። አሁን በተጨባጭ እነ ዋስይሁን አመኑ የሰጧቸውን ፖለቲካዊ ተልዕኮ ለመፈጸም የማንም ቋንቋ ያልሆነውን ግዕዝን ማጥፋት አለብን ብለው ዘመቻ ጀምረዋል። ጥቂት ደጋፊዎቻቸውንም ሰብሰብው አስጨብጭበዋል። ምንም እንኳን ቅዱስ ሲኖዶስ፣መንግስትና አፈንጋጭ ጳጳሳቱ የተስማሙበትን ሳይሸራረፍ ተቀብለናል ብለው የጋራ መግለጫ ቢያወጡም፣ በትረ ሙሴ ስለያዙ ከገበያ የተገዛ የጳጳሳትን አስኬማ ስለደፉ እና ሙስሊምና መናፍቅ ለፖለቲካ ፍጆታ በመንግስት ድጋፍ ወጥቶ ስለተቀበላቸው፣ “ካፈርኩ አይመልሰኝ” በማለት በወረራ የያዙትን መንበረ ጵጵስና አልለቅም ሲሉ ተደምጠዋል።

ለሚያስተውል የትኛውም ምዕመን እንዲህ እንዲህ እናደርግላችኋለን በማለት ከሚዋሹት ውሸት በላይ ከሥራቸው ብዙ መማር ስለሚቻል ምዕመናኑ ወደ ቀልባቸው ተመልሰው ከእነዚህ አቶዎች እጅ መስቀል እንዳይሳለም እነሱ በሚገኙበት አጥብያ ባለመገኘት የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ ሊያከብር ይገባል። መልዕክታችን ነው።

    ቋንቋ አንዳችን ከሌላችን ጋር እንግባባበት ዘንድ ከእግዚአብሔር የተሰጠን የመግባብያ መሳርያ ነው። አንድ ቋንቋ ከሌላው ቋንቋ የሚበልጥበት አንዳች ምክንያት የለም። እርኩስና ቅዱስ የሚባል ቋንቋ የለም። ቋንቋ በጠባዩ ባለቤት የለውም ይባላል። ምክንያቱም ቋንቋ በመወለድ/በዘር/ የሚወረስ ሳይሆን በትምህርትና በልምምድ የሚገኝ ክህሎት ነው። ለዚህም ማሳያ የሚሆነው አንድ ከጉራጌ ቤተሰብ የተወለደ ህጻን ትግራይ ክልል ውስጥ ቢያድግ ያለጥርጥር የአፍ መፍቻ ቋንቋው ትግርኝ እንጂ ጉራግኛ ስለማይሆን፤

ማንኛውም ሰው በአፍ መፍቻ ቋንቋው ወንጌልን መማሩ የሚጠቅመው “ሒዱና ዓለምን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችሁ ደቀመዛሙርት አድርጓቸው” ያለውን የጌታ ቃል መፈጸም ስለሆነ በቀዳሚነት ቤተክርስቲያንን ነው። በሐዋርያዊ ተልዕኮ ትምህርቷም ውስጥ አማኞችን በሚሰሙት ቋንቋ ማስተማር አጽንዖት የሚሰጠው የትምህርት ክፍል ሆኖ እናገኘዋለን። በዚህ ብዥታ ያለው አንድም ሰው ያለ አይመስለኝም። ነገር ግን በቋንቋ ማስተማርን እንደምክንያት ወስዶ ሌላ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ማጃመል ግን እንኳንስ ለዓለም ሞቼያለኹ ከሚል መነኩሴ አይደለም ከየትኛውም ኦርቶዶክሳዊ አማኝ የሚጠበቅ አይደለም። ስለሆነም እነኚህ አካላት ከብዙ መመዘኛ አንጻር እንኳንስና ጳጳስ ቄስ ለመባል ብቁ ስላልሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ ከስህተት እንይወድቅ በጥንቃቄ ጉዳያቸውን ማየት ይኖርበታል እንላለን። ይቆየን።

 

በሲሞን መንገድ ላይ ተገኙት “አባ” ወ/ኢየሱስ ኢፋ (ፍቅሩ ኢፋ) - ክፍል አንድ

 


በህገ ወጥ መንገድ ከተሾሙት የጨረቃ ጳጳሳት ውስጥ አንዱ የቀድሞው አባ ወ/ኢየሱስ ኢፋ የአሁኑ ፍቅሩ ኢፋ ናቸው። እኚህ የቀደሞው አባት የአሁኑ አቶ ፍቅሩ መንፈሳዊ ትምህርታቸውን የጀመሩት በቂልጡ ካራ አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ገዳም ነው። ቂልጡ ካራ አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ገዳም በምዕራብ ወለጋ ዞን የምትኝ የወረዳ ከተማ ስትሆን ገዳሟ የተመሠረተው በተዐምር ነው። እግዚአብሔር የለም የሚለው የደርግ መንግስት ተወግዶ ኢሀዴግ ሀገሪቱን ሲቆጣጠር አብዛኞቹ ወጣቶች ወደ ቤተክርስቲያን የተመለሱበት ጊዜ ነበር። ከዚህም ሌላ መናፍቃኑ በመንግስት ለውጥ ጊዜ የሚፈጠሩ ግርግሮችን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም “ኦርቶዶክስ ትክክል አይደለችም” ብለው በድፍረት ይሰብኩና በጎችን ከመንጋው ለይተው ያስኮበልሉ ስለነበረ፤ በሃይማኖታቸው ፍቅር የሚቃጠሉ ወጣቶች በተቃራኒው መልስ ለመስጠት እና አጽራረ ቤተክርስቲያንን እንዲያስታግስ ሱባኤ መያዝ ጀመሩ።

እነዚህ ወጣቶች ቅዱስ ዳዊት “የቤትህ ቅናት በልታኛለች” እንዳለው ለሃይማኖታቸው ካላቸው ቅንአት የተነሳ የሚያደርጉት እንጂ የሃይማኖት ትምህርት እውቀት ኖሯቸው አልነበረም። ከዚህም የተነሳ ይመስላል አንዳንዶችን ርኩስ መንፈስ የብርሃን መልዐክ መስሎ ይታያቸው የነበረው። በቂልጡ ካራ የነበረው ክስተት ግን እጅግ በጣም የተለየ እንደነበረ በቦታው የነበሩ ወንድሞች እንዲህ ይተርካሉ፡-
አንዲት እህት ነበረች። ይህች እህት ፊደል ስላልቆጠረች መጻፍም ሆነ ማንበብ አትችልም። ቢሆንም በሃይማኖት ጠንካራ ከሚባሉ እና በመንፈሳዊ አገልግሎታቸው ከሚታወቁት እህቶች አንዷ ነበረች። ከእለታት በአንድ ቀን መልዐኩ ቅዱስ ገብርኤል ተገልጾልኛል፣መጻፍና ማንበብም ችያለኹ ትልና እነ ኦርዶፋን ታስገርማቸዋለች። እነ ኦርዶፋም በድፈረቷ ተገርመው መጽሐፍ ሰጥተው አንብቢ ቢሏት ተቀብላቸው አንበለበለችው። ይባስ ብላም እሷ ከመጽሐፍ ቅዱሱ ጀርባ ሆና መጽሐፉን እንዲገልጡ ታዛቸውና የከፈቱትን የመጽሐፍ ቅዱስ ምዕራፍና ቁጥር ነግራ ቃሉን በትክክል ታነብላቸው ያዘች።
በዚህ እጅግ በጣም የተገረሙት እነ ኦርዶፋ በማመን እና ባለማመን መካከል ሆነው ሲወዛገቡ አውቃ ካላመናችሁ ምልክት ልስጣችኹ በማለት የአሁኑ ቄስ የያኔው ዲ/ን በዳሳ በወቅቱ መንዲ ነበር። እሷም “በዳሳ አሁን ያለው መንዲ ነው። የሚመጣውም በአቶ እከሌ መኪና ነው። የሚወርደውም/ቦታውን ጠቅሳ/ እዚህ ቦታ ላይ ነው። ከተጠራጠራችኹ ሔዳችኹ ቆማችኹ አረጋግጡ። በማለት ላከቻቸው። እነሱም በጀ ብለው ኼደው ሲያጣሩ ዲ/ን በጻሳ በተባለው መኪና፣በተባለው ሰዓት እና ቦታ ሲወርድ አዩት። እውነት ለመናገር ለአኹኑ መናፍቃን ሰይጣን እንዲች ያለች ተዐምር እንዲያሳዩ ቢፈቅድላቸው አያኖሩንም ነበር!! ከዚህም የተነሳ ወንድም ኦርዶፋ እና ጥቂት ሰዎች ብቻ ተጠራጥረው እግዚአብሔር ምስጢሩን እንዲገልጽላቸው ሱባኤ ሲይዙ፣ሌሎች ከዲያቆን እስከ ቄስ የምታሳያቸውን ተዐምራት እያዩ ተከተሏት። ይህ በጊዜው ምንም የሃይማኖት ትምህርት እወቀት ላልነበረው የትኛውም ሰው አንዳች መንፈስ ቢገልጽላት ነው እንጂ በስጋና ደም ጥበብ አይደለም ብሎ ቢያምን አይፈረድበትም። ሰይጣን ግን የብርሃን መልዐክ መስሎ መገለጹ፣መጽሐፍ ቅዱስን መጥቀሱ በጌታም ጊዜ የነበረ ልማዱ መሆኑን የተገነዘቡት ሰይጣንነቱ በተገለጸ ጊዜ ነው።
ዝናዋም በመላዋ ቂልጡ ካራ ናኘ። አጫሽ፣ ቃሚ፣ ጠጪ የነበረው የቂልጡ ካራ ወጣት ተዓምር ለማየት ተንጋጋ። መሠረታቸው ተዐምር የሆነው መናፍቃንም በቂልጡካራ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን አዳራሽ የሚደረገውን ተዐምር ለማየት ተሰበሰቡ። እሷም በጴንጤኛ ሙድ “አንተ ሲጃራ አጫሽ ነህ፣አንተ ዝሙት ሰርተሀል ወዘተ እያለች ትክክለኛ ግብራቸውን መናገር ያዘች። ግልብጥ ብሎ የወጣውም ሕዝብ የስነምግባር ጉድለት ያለባቸውን ወጣቶች ስትገስጽ እና እነሱም አምነው ሲንበረከኩ በእውነትም መላኩ ተገልጾላት ነው ብለው በሙሉ ልብ አመኑ። ይህችም እህት በሰይጣን ማታለል የወደቀች መሆኗን ስላልተገነዘበች ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ንዳ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተወህዶ ቤተክርስቲያን ተደርጎ በማያውቅ መልኩ ካህናት አባቶችን አስቀምጣ ቡራኬ መስጠትን ዋና ሥራዋ አደረገች። ስብከተ ወንጌሉንም የግሏ አደረገች። እንዲያውም ከዕለታት ባንድ ቀን ስትፀልይ ከመሬት ከፍ ብላ ተንሳፋ እንደነበር ሰምተናል። ሆኖም ግን አንድ አባት/መሪጌታ ናቸው ይባላል/ በድርጊቱ በጣም እያዘኑ ግን ከጉባኤው የማይለዩ እና ሁል ጊዜም ይጸልዩ ስለነበር እንደልማዷ ሕዝቡ አራሹን ግጥም ብሎ ከአፍ እሰከ ገደፉ ሞልቶ ባለበት መድረክ ይዛ እጸልያለኹ፣አስተምራለኹ፣ትንቢት እናገራለኹ ስትል ድንገት በሙሉ ቁመቷ መድረኩ ላይ ትዘረራለች። ትልቁን አዳራሽ ሞልቶ ይከታተል የነበረው ምዕመን ተደናገጠ። መምህሩም የእግዚአብሔር ቀን እንደደረሰ፣እውነታውም የሚገለጽበት ጊዜው መሆኑን ስለተገነዘቡ ወደ መድረኩ ወጥተው ነብይ ነኝ ትል የነበረው እህት ማጥመቅ ሲጀምሩ ያደረባት ጋኔን መጮህ ያዘ። ተንፈራግጦ ላይመለስ ምሎም ይኼዳል። ተዐምር ለማየት የመጣው መናፍቅ እና የስም ኦርቶዶክስ ሁላ በእውነተኛው የእግዚአብሔር ሥራ ተደሞ ክርስቲያን የነበሩት በእምነታቸው ፀኑ፣መናፍቃን ወደመንጋው ተመለሱ። ይህንን ታሪክ የዛሬውን አያርገውና! ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ወደ ምዕራብ ወለጋ ለሐዋርያዊ ጉዞ በወጣበት ጊዜ ስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ ላይ እንደዘገበው አስታውሳለኹ።
አሁን ለእነ ኦርዶፋ ሰፊ የሥራ በር ተከፍቶላቸዋል። የተመለሰውን አስተምሮ የማጽናት፣ንሰሐ ያልገባውን አስተምሮ ንሰሐ ገብቶ ስጋ ወደሙ እንዲቀበሉ ማድረግ። እነሱም አልሰነፉም። ጊዜም አላባከኑም። በእግዚአብሔር ቸርነት ሴባኤያቸው ውጤት ስላመጣ በእግዚአብሔር ቤት እንዲተከሉ ረዳቸው። እነሆ እስከ ዛሬ ድረስ ሳይወላውሉ ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ርትዕት መሆኗን አምነው ባሉበት ጸንተው አገልግሎታቸውን ሳያስታጉሉ እየፈጸሙ ይገኛሉ።
በዚህ መንገድ የመጣውን ምዕመን በቋንቋው የሚያስተምረው፣ንሰሐ የሚሰጠው፣ቀድሶ የሚያቆርበው ካህንና መምህራንን ማፍራት አማራጭ የሌለው መፍትኼ መሆኑን በማኅበረ ቅዱሳን የነቀምቴ ንዑስ ማእከል፣አሶሳ ንዑስ ማእከል እና በግምቢ ወረዳ ማእከል/የነቀምቴ ረዳት ንዕስ ማእከል/ ያሉ ወንድም እህቶች ከኪሳቸው ገንዘብ በማዋጣት መምህር በመቅጠር የአብነት ትምህርት እንዲጀመር መሠረት ጣሉ። በዚህም እግዚአብሔር ይመስገን ብዙ ፍሬ ማፍራት ተችሏል።
በኋላም አገልግሎቱ እንዲሰፋ እና ቀጣይነቱም እንዲረጋገጥ ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል ሙሉ ኃላፊነቱን እንዲወስድ ተደረገ። ማኅበሩም በገዳማት እና አብነት ትምህርት ቤቶች ዋና ክፍል በኩል ፕሮጄክቶችን በመቅረጽ በጎ አድራጊ ምዕመናን በማስተባበር ከምዕራብ ወለጋ፣ምስራቅ ወለጋ፣ቤኔሻንጉል ጉምዝ እና ጋምቤላ ደቀ መዛሙርትን ተቀብሎ በማስተማር ሰፊ ሐዋርያዊ ተልዕኮውን ተወጥቷል። እየተወጣም ይገኛል።
እነ አባ ወ/ኢየሱስ ኢፋ ከፊደል ቆጠራ እስከ ደረሱበት የትምህርት ሰረጃ የተማሩት በዚሁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ነው። በገዳም ቆይታቸውም ንጽህናቸውን ጠብቀው፣በትምህርት እራሳቸውን አሳድገው እንደ ብጹዑ አቡነ ሔኖክ ለማዕረገ ጵጵስና እንዲደርሱ ልዩ እንክብካቤ ይደረግላቸው እንደነበረ ከምዕራብ ወለጋ ያገኘነው መረጃ ያረጋግጣል። ግና ምን ያደርጋል! “የት ይደርሳል የተባለ ባሕር ዛፍ ቀበሌ ቆረጠው።” እንደተባለ በሲሞን መንገድ ላይ ተገኙ። ይቆየን እንቀጥላለን።

በሲሞን መንገድ ላይ ተገኙት “አባ” ወ/ኢየሱስ ኢፋ (ፍቅሩ ኢፋ) - ክፍል ሁለት

  እኚህ ሰው የእግዚአብሔርን ጥሪ ተቀብለው መንፈሳዊ ትምህርታቸውን መጀመራቸው አያጠራጥርም። በዚህም የሕይወት ምርጫቸውንም ቅዱስ ጳውሎስ “እንደኔ ብትሆኑ እወዳለኹ” ያለውን ተከትለው በሙሉ ጊዜያቸው እግዚአብሔርን እያመሠ...