Wednesday, January 25, 2023

የውስጥ አርበኛ ሆነው እየሠሩ ያሉት ቀሲስ በላይ መኮንን ወደ ተለያዩ ሃገረ ስብከቶች ሕገወጡን ቡድን እንዳይቀበሉ ተገልጾ የተጻፈውን ደብዳቤ አልፈርምም አሉ፡፡

ከመጀመሪያው ጀምረው የኦሮሚያ ቤተክህነት ካልተመሠረተ ብለው ሲየደራጁ የነበሩት እና ኋላ ጥያቄያችን መልስ አግኝቷል በማለት የጠቅላይ ቤተክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ ሆነው እየሠሩ ያሉት ቀሲስ በላይ መኮንን የውስጥ አርበኛ በመሆን ራሱን ላደራጀው አካል ከፍተኛውን ሚና እየተጫወቱ ሲሆን ከጠቅላይ ቤተክህነት ሕገወጡን አካል እንዳይቀበሉ የሚገልጽ ወደየ ሀገረ ስብከቶች እንዲላኩ የተጻፉ ደብዳቤዎችን አልፈርምም በማለት ተቃሞዋቸውን ከወዲሁ ጀምረዋል፡፡ በቤተ ክህነቱ አስተዳደር ጉባኤ እና በሌሎች ብጹአን አበው የሚደረጉ ሕግን የማስከበር ሥራዎችንም ለሕገወጡ ቡድን ከውስጥ የሚያቀብሉት እሳቸው እንደሆኑ እየተገለጸ ነው፡፡



No comments:

Post a Comment

በሲሞን መንገድ ላይ ተገኙት “አባ” ወ/ኢየሱስ ኢፋ (ፍቅሩ ኢፋ) - ክፍል ሁለት

  እኚህ ሰው የእግዚአብሔርን ጥሪ ተቀብለው መንፈሳዊ ትምህርታቸውን መጀመራቸው አያጠራጥርም። በዚህም የሕይወት ምርጫቸውንም ቅዱስ ጳውሎስ “እንደኔ ብትሆኑ እወዳለኹ” ያለውን ተከትለው በሙሉ ጊዜያቸው እግዚአብሔርን እያመሠ...