Monday, February 20, 2023

በሲሞን መንገድ ላይ ተገኙት “አባ” ወ/ኢየሱስ ኢፋ (ፍቅሩ ኢፋ) - ክፍል ሁለት


 

እኚህ ሰው የእግዚአብሔርን ጥሪ ተቀብለው መንፈሳዊ ትምህርታቸውን መጀመራቸው አያጠራጥርም። በዚህም የሕይወት ምርጫቸውንም ቅዱስ ጳውሎስ “እንደኔ ብትሆኑ እወዳለኹ” ያለውን ተከትለው በሙሉ ጊዜያቸው እግዚአብሔርን እያመሠገኑ ለመኖር ወስነው መንኩሰዋል። ግን ለዓለም አልሞቱም። ከክርስቶስ ፍቅር ይልቅ በዘራቸው ፍቅር ተለከፉ፣ከትህትና ይልቅ ትዕቢትን ገንዘብ አደረጉ። እራስን ዝቅ በማድረግ ከሚገኝ አምላካዊ ጸጋ ይልቅ በሰይጣን መንገድ ሄደው መከበርን ሻቱ፣አቦ አቦ መባል ናፈቃቸው። ስለዚህም በእነ ዋስይሁን አመኑና በገረመው አፈወርቅ ፖለቲካ ተጠለፉ። በአፋን ኦሮሞ እያገለገሉ አይናቸውን በጨው አጥበው “የኦሮሞ ሕዝብ በቋንቋው አይገለገልም።” ብለው ዋሹ። እውነታው ግን የሌላ ብሔር ተወላጅ የሆኑ አገልጋዮችን ማየት አለመፈለጋቸው እንደሆነ አብረዋቸው የኖሩ ሰዎች ጠንቅቀው የሚያውቁላቸው ጾራቸው ነው። 

 እንኳንስና እስከ መመንኮስ የደረሰ አገልጋይ ካህን፤ የትኛውም ኦርቶዶክሳዊ ምዕመን የሰው ልጆችን ልዩነት አክብሮ በሰውነታቸው የሃይማኖት፣የብሔር፣የሀብት፣የዕውቀት ወዘተ ልዩነት ሳያደርግ “ባልንጀራህን እንደራስህ አድርገህ ውደድ” ያለውን የጌታ ቃል እንዲፈጽም ግድ የሚለው ሃይማኖታዊ ህሊና ገንዘብ ያደረገ ነው። እኚህ ሰው ግን በጥላቻ የተሞሉ፣ነፍሰ ገዳዮችን በሀሳብ፣በገንዘብ እና በቁሳቁስ የሚደግፉ፣የኦሮሞ መንግስት ተሹሟል። አሁን ጊዜው የእኛ ነው በማለት ተስፋቸውን ከእግዚአብሔር አንስተው ምድራዊ መንግስትን የተደገፉ አሳዛኝ ሰው ናቸው።

የቀድሞው አባ ወ/ኢየሱስ ኢፋ እጅግ ሲበዛ ክብርን የሚፈልጉ የሁሉ አባት ከመሆን ይልቅ የአንድ ብሔር አባት መሆንና መባል የሚፈልጉ፣እጅግ ሲበዛ እልከኛ፣በድሎ ይቅርታ መጠየቅንም ሆነ ተበድሎ ይቅር ማለትን እንደውርደት የሚቆጥሩ ቅዱስ ጳውሎስ ፡ምናልባት ስለ እናንተ በከንቱ ደክመን ይሆናል።” ብሎ እንደተናገረው በከንቱ የተደከመባቸው ሰው ናቸው። ካላቸው የፖለቲካ አመለካከት የተነሳም በገረመው አፈወርቅ መልማይነት የዋስይሁን አመኑ የፖለቲካ ካድሬ ለመሆን የበቁ የኦሮሞ ነጻውጪ ታጋይ መነኩሴ ናቸው።

እኚህ ሰው ቀሚስ አጥልቀው፣ቆብ ደፍተው፣ጺማቸውን አንዠርገው ሲታዩ ለተመልካች የሃይማኖት አባት ይምሰሉ እንጂ ፈጽሞ ኦርቶዶክሳዊነት ያልገባቸው፣እንዲገባቸውም የማይፈልጉ ሲበዛ በራስ አምልኮ የተጠመዱ እና በድፍረት ሐጢያት ለመስራት ወደኋላ የማይሉ ግብዝ ሰው ናቸው። እውነት ለመናገር እንደነዚህ ያሉ አባቶች/ሙሉ ጊዜያቸውን ሰጥተው ቤተክርስቲያንን ለማገልገል የወሰኑ፣የአብነት ትምህርት በመጠኑም ቢሆን የቀጸሉ/ ሲገኙ እንደ አንድ ልጅ በስስት የሚታዩ የዋሁን የምዕራብ ወለጋ ምዕመናንን በተኩላ ከመነጠቅ የሚያድኑ እውነተኛ እረኞች ይሆናሉ ብሎ ተስፋ ያልጣለባቸው በእነሱም ያልተደሰተ ሃይማኖት ወዳድ ምዕመን እና የቤተክርስቲያን አባት አልነበረም።

ሆኖም ግን እነሱ ፖለቲከኞች በፈጠሩት የጨቋኝ ተጨቋኝ ትርክት አዕምሯቸው የታጠበ ለእውነት ቆሞ ጽድቅን ከመስራት ይልቅ በጎጥ ፖለቲካ ውስጥ ተዘፍቀው እግዚአብሔር የሰጣቸውን ፀጋ ተነጥዋል። ከክብርም ተዋርደዋል። እውነት ለመናገር እነኚህ ሰዎች ምንም የሃይማኖት ጥብቅና የሌላቸው፣እንቆምለታለን የሚሉትን የኦሮሞ ሕዝብ ለማገልገል ዕውቀቱም ፍላጎቱም የሌለቻው ናቸው። ለመንግስትም ሆነ ለእግዚአብሔር ለመታዘዝ ልባቸውን ያከበዱ እልከኞች ናቸው። መንግስትን ያስቀደምኩት በእነሱ እምነት አሁን ላይ ሁሉን አድራጊና ፈጣሪ ምድራዊ መንግስታቸው እንጂ የሰማይ አምላክ አይደለምና ነው።

ሰሞኑን “አይዟችሁ ከጎናችሁ ነኝ አንዳች አትፍሩ።” በማለት የልብ ልብ ሲሰጣቸው የከረመው መንግስት የሾሟቸው ጳጳሳት ይቅርታ ጠይቀው እንዲመለሱ ሲያደርግ፣ጓደኛቸው የቀድሞው አባ ገ/ማርያም “የበሬ ወለደ ተረት” ነው ብለው “መንግስትን ውሸታም ነህ” ሲሉት አላፈሩም። አሁን በተጨባጭ እነ ዋስይሁን አመኑ የሰጧቸውን ፖለቲካዊ ተልዕኮ ለመፈጸም የማንም ቋንቋ ያልሆነውን ግዕዝን ማጥፋት አለብን ብለው ዘመቻ ጀምረዋል። ጥቂት ደጋፊዎቻቸውንም ሰብሰብው አስጨብጭበዋል። ምንም እንኳን ቅዱስ ሲኖዶስ፣መንግስትና አፈንጋጭ ጳጳሳቱ የተስማሙበትን ሳይሸራረፍ ተቀብለናል ብለው የጋራ መግለጫ ቢያወጡም፣ በትረ ሙሴ ስለያዙ ከገበያ የተገዛ የጳጳሳትን አስኬማ ስለደፉ እና ሙስሊምና መናፍቅ ለፖለቲካ ፍጆታ በመንግስት ድጋፍ ወጥቶ ስለተቀበላቸው፣ “ካፈርኩ አይመልሰኝ” በማለት በወረራ የያዙትን መንበረ ጵጵስና አልለቅም ሲሉ ተደምጠዋል።

ለሚያስተውል የትኛውም ምዕመን እንዲህ እንዲህ እናደርግላችኋለን በማለት ከሚዋሹት ውሸት በላይ ከሥራቸው ብዙ መማር ስለሚቻል ምዕመናኑ ወደ ቀልባቸው ተመልሰው ከእነዚህ አቶዎች እጅ መስቀል እንዳይሳለም እነሱ በሚገኙበት አጥብያ ባለመገኘት የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ ሊያከብር ይገባል። መልዕክታችን ነው።

    ቋንቋ አንዳችን ከሌላችን ጋር እንግባባበት ዘንድ ከእግዚአብሔር የተሰጠን የመግባብያ መሳርያ ነው። አንድ ቋንቋ ከሌላው ቋንቋ የሚበልጥበት አንዳች ምክንያት የለም። እርኩስና ቅዱስ የሚባል ቋንቋ የለም። ቋንቋ በጠባዩ ባለቤት የለውም ይባላል። ምክንያቱም ቋንቋ በመወለድ/በዘር/ የሚወረስ ሳይሆን በትምህርትና በልምምድ የሚገኝ ክህሎት ነው። ለዚህም ማሳያ የሚሆነው አንድ ከጉራጌ ቤተሰብ የተወለደ ህጻን ትግራይ ክልል ውስጥ ቢያድግ ያለጥርጥር የአፍ መፍቻ ቋንቋው ትግርኝ እንጂ ጉራግኛ ስለማይሆን፤

ማንኛውም ሰው በአፍ መፍቻ ቋንቋው ወንጌልን መማሩ የሚጠቅመው “ሒዱና ዓለምን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችሁ ደቀመዛሙርት አድርጓቸው” ያለውን የጌታ ቃል መፈጸም ስለሆነ በቀዳሚነት ቤተክርስቲያንን ነው። በሐዋርያዊ ተልዕኮ ትምህርቷም ውስጥ አማኞችን በሚሰሙት ቋንቋ ማስተማር አጽንዖት የሚሰጠው የትምህርት ክፍል ሆኖ እናገኘዋለን። በዚህ ብዥታ ያለው አንድም ሰው ያለ አይመስለኝም። ነገር ግን በቋንቋ ማስተማርን እንደምክንያት ወስዶ ሌላ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ማጃመል ግን እንኳንስ ለዓለም ሞቼያለኹ ከሚል መነኩሴ አይደለም ከየትኛውም ኦርቶዶክሳዊ አማኝ የሚጠበቅ አይደለም። ስለሆነም እነኚህ አካላት ከብዙ መመዘኛ አንጻር እንኳንስና ጳጳስ ቄስ ለመባል ብቁ ስላልሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ ከስህተት እንይወድቅ በጥንቃቄ ጉዳያቸውን ማየት ይኖርበታል እንላለን። ይቆየን።

 

በሲሞን መንገድ ላይ ተገኙት “አባ” ወ/ኢየሱስ ኢፋ (ፍቅሩ ኢፋ) - ክፍል አንድ

 


በህገ ወጥ መንገድ ከተሾሙት የጨረቃ ጳጳሳት ውስጥ አንዱ የቀድሞው አባ ወ/ኢየሱስ ኢፋ የአሁኑ ፍቅሩ ኢፋ ናቸው። እኚህ የቀደሞው አባት የአሁኑ አቶ ፍቅሩ መንፈሳዊ ትምህርታቸውን የጀመሩት በቂልጡ ካራ አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ገዳም ነው። ቂልጡ ካራ አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ገዳም በምዕራብ ወለጋ ዞን የምትኝ የወረዳ ከተማ ስትሆን ገዳሟ የተመሠረተው በተዐምር ነው። እግዚአብሔር የለም የሚለው የደርግ መንግስት ተወግዶ ኢሀዴግ ሀገሪቱን ሲቆጣጠር አብዛኞቹ ወጣቶች ወደ ቤተክርስቲያን የተመለሱበት ጊዜ ነበር። ከዚህም ሌላ መናፍቃኑ በመንግስት ለውጥ ጊዜ የሚፈጠሩ ግርግሮችን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም “ኦርቶዶክስ ትክክል አይደለችም” ብለው በድፍረት ይሰብኩና በጎችን ከመንጋው ለይተው ያስኮበልሉ ስለነበረ፤ በሃይማኖታቸው ፍቅር የሚቃጠሉ ወጣቶች በተቃራኒው መልስ ለመስጠት እና አጽራረ ቤተክርስቲያንን እንዲያስታግስ ሱባኤ መያዝ ጀመሩ።

እነዚህ ወጣቶች ቅዱስ ዳዊት “የቤትህ ቅናት በልታኛለች” እንዳለው ለሃይማኖታቸው ካላቸው ቅንአት የተነሳ የሚያደርጉት እንጂ የሃይማኖት ትምህርት እውቀት ኖሯቸው አልነበረም። ከዚህም የተነሳ ይመስላል አንዳንዶችን ርኩስ መንፈስ የብርሃን መልዐክ መስሎ ይታያቸው የነበረው። በቂልጡ ካራ የነበረው ክስተት ግን እጅግ በጣም የተለየ እንደነበረ በቦታው የነበሩ ወንድሞች እንዲህ ይተርካሉ፡-
አንዲት እህት ነበረች። ይህች እህት ፊደል ስላልቆጠረች መጻፍም ሆነ ማንበብ አትችልም። ቢሆንም በሃይማኖት ጠንካራ ከሚባሉ እና በመንፈሳዊ አገልግሎታቸው ከሚታወቁት እህቶች አንዷ ነበረች። ከእለታት በአንድ ቀን መልዐኩ ቅዱስ ገብርኤል ተገልጾልኛል፣መጻፍና ማንበብም ችያለኹ ትልና እነ ኦርዶፋን ታስገርማቸዋለች። እነ ኦርዶፋም በድፈረቷ ተገርመው መጽሐፍ ሰጥተው አንብቢ ቢሏት ተቀብላቸው አንበለበለችው። ይባስ ብላም እሷ ከመጽሐፍ ቅዱሱ ጀርባ ሆና መጽሐፉን እንዲገልጡ ታዛቸውና የከፈቱትን የመጽሐፍ ቅዱስ ምዕራፍና ቁጥር ነግራ ቃሉን በትክክል ታነብላቸው ያዘች።
በዚህ እጅግ በጣም የተገረሙት እነ ኦርዶፋ በማመን እና ባለማመን መካከል ሆነው ሲወዛገቡ አውቃ ካላመናችሁ ምልክት ልስጣችኹ በማለት የአሁኑ ቄስ የያኔው ዲ/ን በዳሳ በወቅቱ መንዲ ነበር። እሷም “በዳሳ አሁን ያለው መንዲ ነው። የሚመጣውም በአቶ እከሌ መኪና ነው። የሚወርደውም/ቦታውን ጠቅሳ/ እዚህ ቦታ ላይ ነው። ከተጠራጠራችኹ ሔዳችኹ ቆማችኹ አረጋግጡ። በማለት ላከቻቸው። እነሱም በጀ ብለው ኼደው ሲያጣሩ ዲ/ን በጻሳ በተባለው መኪና፣በተባለው ሰዓት እና ቦታ ሲወርድ አዩት። እውነት ለመናገር ለአኹኑ መናፍቃን ሰይጣን እንዲች ያለች ተዐምር እንዲያሳዩ ቢፈቅድላቸው አያኖሩንም ነበር!! ከዚህም የተነሳ ወንድም ኦርዶፋ እና ጥቂት ሰዎች ብቻ ተጠራጥረው እግዚአብሔር ምስጢሩን እንዲገልጽላቸው ሱባኤ ሲይዙ፣ሌሎች ከዲያቆን እስከ ቄስ የምታሳያቸውን ተዐምራት እያዩ ተከተሏት። ይህ በጊዜው ምንም የሃይማኖት ትምህርት እወቀት ላልነበረው የትኛውም ሰው አንዳች መንፈስ ቢገልጽላት ነው እንጂ በስጋና ደም ጥበብ አይደለም ብሎ ቢያምን አይፈረድበትም። ሰይጣን ግን የብርሃን መልዐክ መስሎ መገለጹ፣መጽሐፍ ቅዱስን መጥቀሱ በጌታም ጊዜ የነበረ ልማዱ መሆኑን የተገነዘቡት ሰይጣንነቱ በተገለጸ ጊዜ ነው።
ዝናዋም በመላዋ ቂልጡ ካራ ናኘ። አጫሽ፣ ቃሚ፣ ጠጪ የነበረው የቂልጡ ካራ ወጣት ተዓምር ለማየት ተንጋጋ። መሠረታቸው ተዐምር የሆነው መናፍቃንም በቂልጡካራ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን አዳራሽ የሚደረገውን ተዐምር ለማየት ተሰበሰቡ። እሷም በጴንጤኛ ሙድ “አንተ ሲጃራ አጫሽ ነህ፣አንተ ዝሙት ሰርተሀል ወዘተ እያለች ትክክለኛ ግብራቸውን መናገር ያዘች። ግልብጥ ብሎ የወጣውም ሕዝብ የስነምግባር ጉድለት ያለባቸውን ወጣቶች ስትገስጽ እና እነሱም አምነው ሲንበረከኩ በእውነትም መላኩ ተገልጾላት ነው ብለው በሙሉ ልብ አመኑ። ይህችም እህት በሰይጣን ማታለል የወደቀች መሆኗን ስላልተገነዘበች ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ንዳ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተወህዶ ቤተክርስቲያን ተደርጎ በማያውቅ መልኩ ካህናት አባቶችን አስቀምጣ ቡራኬ መስጠትን ዋና ሥራዋ አደረገች። ስብከተ ወንጌሉንም የግሏ አደረገች። እንዲያውም ከዕለታት ባንድ ቀን ስትፀልይ ከመሬት ከፍ ብላ ተንሳፋ እንደነበር ሰምተናል። ሆኖም ግን አንድ አባት/መሪጌታ ናቸው ይባላል/ በድርጊቱ በጣም እያዘኑ ግን ከጉባኤው የማይለዩ እና ሁል ጊዜም ይጸልዩ ስለነበር እንደልማዷ ሕዝቡ አራሹን ግጥም ብሎ ከአፍ እሰከ ገደፉ ሞልቶ ባለበት መድረክ ይዛ እጸልያለኹ፣አስተምራለኹ፣ትንቢት እናገራለኹ ስትል ድንገት በሙሉ ቁመቷ መድረኩ ላይ ትዘረራለች። ትልቁን አዳራሽ ሞልቶ ይከታተል የነበረው ምዕመን ተደናገጠ። መምህሩም የእግዚአብሔር ቀን እንደደረሰ፣እውነታውም የሚገለጽበት ጊዜው መሆኑን ስለተገነዘቡ ወደ መድረኩ ወጥተው ነብይ ነኝ ትል የነበረው እህት ማጥመቅ ሲጀምሩ ያደረባት ጋኔን መጮህ ያዘ። ተንፈራግጦ ላይመለስ ምሎም ይኼዳል። ተዐምር ለማየት የመጣው መናፍቅ እና የስም ኦርቶዶክስ ሁላ በእውነተኛው የእግዚአብሔር ሥራ ተደሞ ክርስቲያን የነበሩት በእምነታቸው ፀኑ፣መናፍቃን ወደመንጋው ተመለሱ። ይህንን ታሪክ የዛሬውን አያርገውና! ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ወደ ምዕራብ ወለጋ ለሐዋርያዊ ጉዞ በወጣበት ጊዜ ስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ ላይ እንደዘገበው አስታውሳለኹ።
አሁን ለእነ ኦርዶፋ ሰፊ የሥራ በር ተከፍቶላቸዋል። የተመለሰውን አስተምሮ የማጽናት፣ንሰሐ ያልገባውን አስተምሮ ንሰሐ ገብቶ ስጋ ወደሙ እንዲቀበሉ ማድረግ። እነሱም አልሰነፉም። ጊዜም አላባከኑም። በእግዚአብሔር ቸርነት ሴባኤያቸው ውጤት ስላመጣ በእግዚአብሔር ቤት እንዲተከሉ ረዳቸው። እነሆ እስከ ዛሬ ድረስ ሳይወላውሉ ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ርትዕት መሆኗን አምነው ባሉበት ጸንተው አገልግሎታቸውን ሳያስታጉሉ እየፈጸሙ ይገኛሉ።
በዚህ መንገድ የመጣውን ምዕመን በቋንቋው የሚያስተምረው፣ንሰሐ የሚሰጠው፣ቀድሶ የሚያቆርበው ካህንና መምህራንን ማፍራት አማራጭ የሌለው መፍትኼ መሆኑን በማኅበረ ቅዱሳን የነቀምቴ ንዑስ ማእከል፣አሶሳ ንዑስ ማእከል እና በግምቢ ወረዳ ማእከል/የነቀምቴ ረዳት ንዕስ ማእከል/ ያሉ ወንድም እህቶች ከኪሳቸው ገንዘብ በማዋጣት መምህር በመቅጠር የአብነት ትምህርት እንዲጀመር መሠረት ጣሉ። በዚህም እግዚአብሔር ይመስገን ብዙ ፍሬ ማፍራት ተችሏል።
በኋላም አገልግሎቱ እንዲሰፋ እና ቀጣይነቱም እንዲረጋገጥ ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል ሙሉ ኃላፊነቱን እንዲወስድ ተደረገ። ማኅበሩም በገዳማት እና አብነት ትምህርት ቤቶች ዋና ክፍል በኩል ፕሮጄክቶችን በመቅረጽ በጎ አድራጊ ምዕመናን በማስተባበር ከምዕራብ ወለጋ፣ምስራቅ ወለጋ፣ቤኔሻንጉል ጉምዝ እና ጋምቤላ ደቀ መዛሙርትን ተቀብሎ በማስተማር ሰፊ ሐዋርያዊ ተልዕኮውን ተወጥቷል። እየተወጣም ይገኛል።
እነ አባ ወ/ኢየሱስ ኢፋ ከፊደል ቆጠራ እስከ ደረሱበት የትምህርት ሰረጃ የተማሩት በዚሁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ነው። በገዳም ቆይታቸውም ንጽህናቸውን ጠብቀው፣በትምህርት እራሳቸውን አሳድገው እንደ ብጹዑ አቡነ ሔኖክ ለማዕረገ ጵጵስና እንዲደርሱ ልዩ እንክብካቤ ይደረግላቸው እንደነበረ ከምዕራብ ወለጋ ያገኘነው መረጃ ያረጋግጣል። ግና ምን ያደርጋል! “የት ይደርሳል የተባለ ባሕር ዛፍ ቀበሌ ቆረጠው።” እንደተባለ በሲሞን መንገድ ላይ ተገኙ። ይቆየን እንቀጥላለን።

Sunday, February 5, 2023

የግድያ አዋጅ የተላለፈበት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ


ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለካቢኔያቸው በሰላምና ሃይማኖታዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሰጡት ማብራሪያ ተብሎ ጥር 23 ቀን 2015 ዓ.ም በተለያዩ የመንግሥት ሚዲያዎች ሲተላለፍ ነበር። ማብራሪያው ግልጽ አለመሆኑ ብቻ ሳይሆን ይህን ከመሪ የማይጠበቅ ንግግር በብሮድካስት ማስተላለፍ ለምን እንደተፈለገም ግልጽ አይደለም። ማብራሪያው ያለ መረጃና ማስረጃ የቀረበ ማስፈራሪያ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩከተናገሩት መረዳት የሚቻለው የእነ ደመላሽ/አካለወልድ ሞጎር የሐሰት ሢመተ ጵጵስና በመንግሥት ውሳኔ የተፈጸመ መሆኑን ብቻ ነው። በዚህ በኩል ስለሰጡን ግልጽና እውነተኛ መረጃ ሳናመሰግን አናልፍም። ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ቤተ ክርስቲያን አገር ናት” በማለት ለቤተ ክርስቲያን በጎ ዐሳብ እንዳላቸው በማስመሰል እንዳልተናገሩ፣ ዛሬ አገር አፍራሾች ሲነሡባት አገር ናት ያሏትን ቤተ ክርስቲያን ከመጠበቅ ይልቅ ከአፍራሾች ጎን መሰለፋቸው ቀድሞውንም ለአቅርቦተ ኦርቶዶክሳውያን ብቻ የተናገሩት መሆኑን ያስረግጣል። እንዲያውም መመሪያ እና ውሳኔ በሚመስል መልኩ ለቤተ ክርስቲያን ዐዲስ ቀኖና ለመሥራት ሲዳዳቸው ነበር። በአጠቃላይ ማብራሪያው ያለዝግጅት የተነገረ፣ በተፋልሶ የተሞላ፣ የሕገወጡ ቡድን እንቅስቃሴ መንግሥት መር መሆኑን ያረጋገጠ፣ የቤተ ክርስቲያንን ሕጋዊ ሰውነት የሚጋፋ፣ ለቤተ ክርስቲያን ያላቸውን ጥላቻና ንቀት ያጋለጠ እና እንደ አገር መሪ ሳይሆን እንደሕገወጥ ቡድኑ ቃል አቀባይ የቀረበ ነበር ማለት ይቻላል። ከዚህ አንጻር መሠረታዊ የሚባሉት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግሮች ላይ ጥያቄና ትችት ማቅረብ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።


1.  መንግሥት ለቤተ ክርስቲያን ስላደረገው ድጋፍ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተደጋጋሚ ሲናገሩ የተሰሙት እርሳቸውና መንግሥታቸው ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ያላደረጉላት ነገር እንደሌለ ነው። ሲኖዶስን እንዳስታረቁ፣ የተወረሱ ሕንፃዎችን እንደመለሱ፣ በሚሊዮን ካሬ ሜትር ይዞታ እንደሰጡ፣ ለቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ዕድሳት ከፈረንሣይ መንግሥት ፈንድ እንዳገኙ፣ በአቡዳቢ ይዞታ እንዲኖራት እንዳደረጉ በድፍረት ሲናገሩ ነበር። እውነታው ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሁሉም ጉዳዮች ላይ የድል አጥቢያ አርበኛ ሆነው ከመከሰታቸውና ክሬዲቱን ለመውሰድ ከመፈለጋቸው ውጪ “ከነገሥታቱ በኋላ እንደ እኔ መንግሥት በጎ ያደረገ የለም” የሚል ፉከራ ለማስተጋባት የሚያስችል አስተዋፅዖ የሌላቸው መሆኑ ነው። በተለይም በውጪ በሚኖሩት አባቶችና በቅዱስ ሲኖዶስ መካከል የተደረገውን ዕርቅ ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ እንደሚረዳው ቀድሞ የተጀመረና ልዑካንን በመላክ ብዙ የተደከመበት ጉዳይ ነበር። የዕርቅ ፍላጎቱም የአባቶች እንጂ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የድካም ውጤት አለመሆኑ ፀሐይ የሞቀው ሐቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀድሞ የነበረው መንግሥት እንደሚያደርገው እንቅፋት አለመሆናቸው የሚያስመሰግናቸው መሆኑ አልተካደም። ለዚህ ደግሞ ቤተ ክርስቲያን ተገቢውን ምናልባትም ከሚገባቸው በላይ ዕውቅና ሰጥታለች።

“ደርግ ፓትርያርክ ሲገድል፣ ኢሕአዴግ ሲያሳድድ እኛ ግን መግደልም ማሳደድም ትክክል አይደለም ብለን በውጪና በውስጥ ያሉ አባቶችን በማስታረቅ አግዘናል” ብለዋል። እርቅንና የአገር አንድነትን በመሻት የተፈጸመ ከነበረ መልካም ነው። ነገር ግን “ደርግ ፓትርያርኩን የገደላቸው ለንጉሡ ቃለ መሐላ ፈጽመው የተሾሙ ስለነበሩ አብረው መሔድ ባለመቻላቸው ነው፤ ኢሕአዴግም በወቅቱ የነበሩትን ፓትርያርክ ያሳደዳቸው በደርግ የተሾሙ ስለነበሩ አብረው መሔድ ባለመቻላቸው ነው” በማለት የሰጡት ማብራሪያ የመንግሥታቱን ድርጊት ትክክለኛነት የሚያጸድቅ እንጂ የጸፈጸመውን ግፍ የሚያወግዝ አይደለም። የንግግሩ ዐውድ ችግሩ የፓትርያርኮች እንጂ የመንግሥታቱ ሆኖ አልቀረበም። የእርስዎ መንግሥትም ፓትርያርክ ከመግደልና ከማሳደድ ቤተ ክርስቲያኗን ራሷን ማሳደድ የሚል መርሕ መከተሉ ከሌሎች የከፋ ቢያደርገው እንጂ የሚሻል ሊሆን አይችልም። እንዲያውም ሌሎች መንግሥታት በጅራፍ እንደገረፏችሁ እኔ ደግሞ በጊንጥ እነድፋችኋለሁ ያለ ነው የሚመስለው። ተደረጉ የተባሉት ጉዳዮችም የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት እንጂ ለቤተ ክርስቲያን ታስበው የተደረጉ እንዳልሆኑ አሁን ላይ በቤተ ክረስቲያን ላይ እየተደረገ ካለው መረዳት ይቻላል። ስለሆነም በዕርቁ ጉዳይ ሊወስዱት የሚፈልጉትን ድካም አልባ ዋጋ ወስደው እንደጨረሱ ስንገልጽ በትህትና ነው። 

የቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያንን በተመለከተ የተናገሩት ግን አይደለም ዓለማዊ ነኝ ከሚል መንግሥት መሪ ከኦርቶዶክስ በአንጻር የተቋቋመ ከሃይማኖታዊ መንግሥት መሪ እንኳን የሚጠበቅ አይደለም። የቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት በዓለም ቅርስነት የተመዘገቡ ከአገር አልፈው ዓለም አቀፍ ሀብቶች ናቸው። ለዚህ ቅርስ ዕድሳትና ጥገና ለማድረግ ኦርቶዶክስ ወይም ኢትዮጵያዊ መሆን አያስፈልግም። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግን የተናገሩት ከዚህ ፈጽሞ የራቀ ነው። በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 41 (9) መንግሥት የባህልና የታሪክ ቅርሶችን የመንከባከብ ኃላፊነት እንዳለበት ተደንግጓል። ይህን ኃላፊነት ለመወጣት የሚፈጸሙ ተግባራት ሁሉ ከችሮታና ከውለታ ወይም ቤተ ክርስቲያንን ከመውደድ ሊቆጠሩ አይገባቸውም። የገዳማቱ ዕድሳት ማድረጊያ ፈንድ ማፈላለግ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሳይሆን አስቀድሞ የተጀመረ ነው። የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን የዕድሳት ፕሮጀክት ስምምነት በተፈረመበት ጥር 26 ቀን 2010 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ አብያተ ክርስቲያኑን ለማደስ እንቅስቃሴ መጀመሩን ከመንግሥት በተጨማሪ ሌሎች አካላትም እንዲሳተፉ ጥሪ በማድረግ ሥራው እንደተጀመረ የሚታወቅ ነው። ያ ማለት ደግሞ ጠቅላይ ሚንስትሩ ወደ ሥልጣን ከመምጣታቸው በፊት መሆኑ ነው፡፡ ይህን እውነት በመጋፋት የተሰጠው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ የአገር መሪነትን ሚና የረሳና የፈንድ ማፈላለግ ሥራው ፈር ቀዳጅ አስመስሎ ያቀረበ ስለሆነ ፈጽሞ አግባብነት ያለው አይደለም።

የደርግ መንግሥት አራት ኪሎ የሚገኙትን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በራሷ ጉልበትና ሀብት ያፈራቻቸውን ሁለት መንትያ ሕንፃዎች ያለአግባብ ወስዶ መቆየቱ ይታወቃል። ቤተ ክርስቲያን በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 398 መሠረት እንደ አንድ ሰው የምትቆጠር እንደመሆኗ ንብረት የማፍራት መብት ያላት ናት። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደ ትልቅ ውለታ የሚገልጹት እነዚህን ንብረትነታቸው የቤተ ክርስቲያን የሆኑ ሕንፃዎችን መመለሳቸውን ነው። የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በተለያዩ የሰበር መዛግብት በሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ያለአግባብ ከአዋጅ ውጪ የተወሰዱ ቤቶችን ለሚመለከተው አካል ጥያቄ በማቅረብ ባለመብት መሆን ይቻላል። ስለሆነም ቤተ ክርስቲያን የራሷን ንብረት በአስተዳደራዊ መፍትሔ ወይም በፍርድ ቤት ውሳኔ ማግኘቷ የተለየ ምስጋና የሚያሻው ጉዳይ ሳይሆን ሕጋዊ መብቷ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአገር መሪና የመንግሥት ባለሥልጣን መሆናቸውን እየረሱት ካልሆነ በስተቀር መንግሥት የሚያስፈልግበት ዋናው ምክንያትም ይህን መሰል ፍትሕን ለማስፈን ነው። ስለሆነም በሕግ የተፈቀዱ መብቶችን ማስከበርና ፍትሕ ማስፈን መንግሥታዊ ግዴታ እንጂ ግለሰባዊ እርዳታ አይደለም። እንዲህ ዐይነቱ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን አድርጌላችሁ መግለጫ ከዕውቀት ማነስ የሚነጭም ሊሆን ይችላል።

2.  ለቤተ ክርስቲያ ስለተሰጣት የአምልኮ ስፍራ

የአምልኮ ሥፍራ አሰጣጥን በተመለከተ መንግሥት ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በማድላት ሰፊ ቦታ እንደተሰጣት የተገለጸበት አግባብ ፈጽሞ ሐሰት ከመሆኑም ውጪ መንግሥት አድሏዊ መሆኑን በግልጽ ያመነበት በመሆኑ ከፖለቲካ እርምት አንጻር እንኳን ተገቢነት የለውም። መረጃው በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አበቤ ተዘጋጅቶ በጠቅላይ ሚኒስትሩም ያለምንም ማጣሪያ የቀረበ መሆኑ ከዚህ በፊትም በብዙ ማስረጃዎች ስለቀረበ ወደዚያ ትንተና መግባት ላያስፈልግ ይችላል። ነገር ግን ቤተ ክርስቲያን የሚገባትን እንጂ የማይገባትን አትጠይቅም፤ አዲስ አበባ ውስጥ ያሏት ይዞታዎችም ካላት ምእመናን አንጻር ፈጽሞ በቂ አይደሉም። ተደረገላት የተባለውም አልተደረገም እንጂ ተደርጎ ቢሆን እንኳን የሚያንስባት እንጂ የሚበዛባት አይደለም። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሌሎች ቤተ እምነቶች የተሰጠው ይዞታ ተደምሮ ለቤተ ክርስቲያን ከተሰጠው ይዞታ 1/3ኛ ያህል ነው ብለዋል። እስኪ እንጠይቅዎ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፡- ይህን የሰጡትን አንድ ሚሊዮን ካሬ ሜትር ይዞታ በማስረጃ ሊያረጋግጡልን ይችላሉ? በእውነት ተሰጥቶ ከሆነም ስትሰጡ ፍትሐዊ ነው ብላችሁ አምናችሁበት ነው? ከሆነ በምን ምክንያት ፍትሐዊ ነው አላችሁ? ፍትሐዊ ካልሆነስ ለምን ሰጣችሁ? በማብራሪያውስ ለሌሎች ቤተ እምነቶች ለእናንተ የተሰጠው ይዞታ ከኦርቶዶክስ አንጻር በጣም ትንሽ ነው በማለት ሲናገሩ ቅሬታ እንደማይፈጥርባቸው በምን መተማመኛ ተናገሩት? ሰጠነው ያሉትንስ ይዞታ ስትሰጡ በምን ማስተር ፕላን ሰጣችሁ? እርስዎ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ሳለ የመሬት አስተዳደር ባለሙያ ሥራ ውስጥ መግባትዎስ ለምን አስፈለገ? በኦርቶዶክስ ላይ ያለዎትን ጥላቻና አድሏዊነት ለመሸፋፈን ያቀረቡት እንጂ በመንግሥትዎ ለቤተ ክርስቲያን የተደረገላት ጥቂት የተደረገባት ግን ብዙ ነው። በተጨማሪም የሌሎች እምነት ሰዎችን በቤተ ክርስቲያን ላይ ለማነሳሳትና ደጋፊ ለማሰባስበ የተደረግ ጥረት መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡

ክፍል ሦስት


3.  ስለ ሕገወጡ እንቅስቃሴ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ የመስጠታቸው ዋናው ምክንያት ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በእነደመላሽ/አካለወልድ አማካኝነት የተፈጸመው መፈንቅለ ሲኖዶስ ነው። እነዚህ አካላት ያለ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅና ፈቃድ ሃይማኖታዊ ቀኖናዊ ጥሰት በመፈጸም “ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት ፈጽመናል” በማለት መግለጫ ሰጥተዋል። ሕገወጥ ድርጊታቸውን ለማጽደቅም ዲያብሎስ በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ አራት ላይ እንደተገለጸው በጥቅስ በማስደገፍ የዋሀንን ለማደናገር ሞክረዋል። ይህ ጉዳይ ሃይማኖታዊ ጉዳይ እንደመሆኑ መጠን መፍትሔ ሊሰጥ የሚገባው በቤተ ክርስቲያን ነው። የጉዳዩ ባለቤት የሆነችው ቤተ ክርስቲያን ደግሞ የተፈጸመው አድራጎት የሃይማኖትና የቀኖና ጥሰት ስለሆነ ሐሳዊ ሢመተ ጵጵስና ሿሚዎቹም ሆኑ ተሿሚዎቹ ተወግዘው ከቤተ ክርስቲያን እንዲለዩ ወስናለች። ይህን ውሳኔ በመቃወም በመንግሥት አካላት የሚሰጥ መግለጫ ሁሉ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 11 የተቀመጠውን የመንግሥትና የሃይማኖት መለያየት መርሕ መጣስና በቤተ ክርስቲያን የውስጥ ጉዳዮች ጣልቃ መግባት ነው። 

ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ጉዳዩን ሁለቱም ወገኖች በመደራደር እንዲፈቱ የሰጠነው ምክር ተቀባይነት አላገኘም፤ የትኛውንም ቡድን አንደግፍም፣ ሁለቱም ወገኖች አባቶቻችን ናቸው፤ በዚህ ጉዳይ ማንም እጁን እንዳያስገባ” በማለት ሕገወጥ ቡድኖችን በቤተ ክርስቲያን አንጻር በአቻ ወንበር በማስቀመጥ ፍላጎታቸው ምን እንደሆነ ገልጸዋል። ክቡር ሆይ! “የትኛውንም ቡድን” ብለው ቤተ ክርስቲያንን ከአንድ ሕገወጥ ቡድን ጋር ማነጻጸርዎ ሳያንስ ሕጋዊ ሰውነት ያላትን ቤተ ክርስቲያን መጠበቅ ግዴታዎ መሆኑን መዘንጋትዎ በእጅጉ ያሳዝናል። የመንግሥት ጽንሰ ሐሳብ የተፈጠረው እያንዳንዱ ሰው ካለው የማይገደብ ነጻነት ሸርፎ ሕግና ሥርዓት አስከባሪ መኖሩን በማመን ጉልበተኞች የደካሞችን፣ ግልፍተኞች የታጋሾችን መብት እንዳይጋፉ ለማድረግ ነው። መንግሥት የተፈጠረበት ዓላማ ሰላምና ደኅንነትን ለማረጋገጥ ነው። የያዙት ሥልጣን ለሕዝብ አገልግሎት፣ ከሕዝብ ያገኙት እንጂ የግልዎ አይደለም። ስለሆነም ቤተ ክርስቲያንን የመደገፍ ሳይሆን የመጠበቅ እና ሕጋዊ መብቷን የማስከበር ግዴታ የመንግሥትዎ መሆኑን ለማስረዳት እንወዳለን። እርስዎ ፍላጎት ባይኖርዎት እንኳን “ማንም እጁን እንዳስገባ” የሚል ትእዛዝ ማስተላለፍዎ በሕግ ተጠያቂነት የሚያመጣ የጥላቻ ንግግር መሆኑን ሊረዱት በተገባ ነበር።

ምናልባት የተፈጠረውን ጉዳይ ምን እንደሆነ ለማስረዳት በቀላል ምሳሌ እንመልከት። ከሁለት ወይም ከሦስት ክልል ከመጡ የፓርላማ ተወካዮች መካከል የተወሰኑ አባላት ለብቻቸው አንድ አዳራሽ ውስጥ ተሰብስበው ያለ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዕውቅናና ውሳኔ አሁን ያለው የፓርላማ ስብስብ ሁሉንም ያማከለ ስላልሆነ ከዛሬ ጀምሮ የፓርላማ አባላት የሚሆኑት እነዚህ ናቸው ብለው አወጁ። ከዚያም ከመረጧቸው ሰዎች ጋር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነን ብለው አስፈጻሚ አካላትን አዋቀሩ። በየክልሉና በየዞኑ የአስፈጻሚ አካላትን ቢሮ በመስበር እየገቡ ከዛሬ ጀምሮ መሪዎቻችሁ እኛ ነን አሉ። እርስዎ ከእነዚህ አካላት ጋር ጦርነት ይገጥማሉ ወይስ በድርድር ተቀብለው የተወካዮች ምክር ቤት እና የሚኒስትሮች ምክር ቤት አባል እንዲሆኑ ይፈቅዳሉ? በቤተ ክርስቲያን ላይ የተፈጸመው ይህ ነው። ሦስት ሕገወጦች ተነሥተው በሌላቸው ሥልጣን ጳጳስ ሾመናል አሉ። እነዚያን ሕገወጥ ተሿሚዎች በየሀገረ ስብከቱ በመመደብ የቤተ ክርስቲያንን መዋቅር በመቆጣጠር ወረራ ፈጸሙ። ይህ ሲሆን ቤተ ክርስቲያን በአገር መንግሥት አለ ብላ በማመን እየተፈጸመ ያለው ሕገወጥ ድርጊት እንዲቆም ለመንግሥት አሳወቀች። መንግሥትም ሕገወጦችን በመደገፍ የቤተ ክርስቲያን አባቶችን በማንገላታትና በማሳደድ ለቤተ ክርስቲያን ጩኸት አሉታዊ ምላሽ ሰጠ። ሕገወጦችን በፓትሮል እያጀበ ወደ ሀገረ ስብከት እያስገባ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትን ከመንበራቸው ማሳደድ ጀመረ። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሕገወጥ ሹመቱ እና በየሀገረ ስብከቱ እየተፈጸመ ያለው ወረራ በመንግሥት ይሁንታ የተፈጸመ መሆኑን በመግለጽ ሌላ አማራጭ መፈለግ እንደሚገባን አሳይተውናል።

ጉዳዩን ቀላል አድርገው ያቀረቡበትም መሠረታዊ ምክንያት የታቀደበትና በመንግሥት በኩል በግድም ቢሆን ተፈጻሚ ለማድረግ እየሠራ ስለሆነ ነው። የቤተ ክርስቲያንን ጩኸት ለመስማት ማንም እጁን እንዳያስገባ ካቢኔዎችዎን ያስጠነቀቁበት መንገድ ልጆቹን የሚቆጣ አባት ይመስሉ ነበር። ሕገወጦችን ለመደገፍ እጅን አስረዝሞ፣ አገር የሠራችን ቤተ ክርስቲያን ሰላምና ደኅንነት ለማስከበር እጅን መሰብሰብ ምንም የሚያስከፍለው ዋጋ እንደሌለ ማሰብዎ አማካሪ አልባ መሆንዎን ወይም ሰነፍ አማካሪ እንዳለዎት ያረጋግጣል። ጌታዋን የተማመነች በግ ሆነው እንጂ እነ አካለወልድ ይህን ቀልድ በራሳቸው ሥልጣን እንደማይሞክሩት ከዚህ በፊት በነበረን ልምድ እናውቃቸዋለን። መንግሥት እጁን ብቻ ሳይሆን ሙሉ አካሉን አስገብቶ አይዟችሁ ባይ ደጀን፣ አዝማች ፊታውራሪ ሆኖ እየሠራ መሆኑን ቀድሞም ከሕገወጦች የፓትሮል እጀባ እና ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት እንግልት አሁንም ከንግግርዎ ተገንዝበነዋል። 

ለይስሙላ እንኳን ሕገወጥ ድርጊቱን ከማውገዝ ይልቅ ሌሎችም እንዲሁ ሲያደርጉ እንደነበር የገለጹት ዐሳብ በእርስዎ አድሮ አካለወልድ እየተናገረ እንጂ ራስዎ የተናገሩት አይመስልም። ውጪ የነበሩት አባቶች ጋር የተፈጸመውን ዕርቅ፣ በትግራይ ክልል የሚኖሩ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሰጡትን መግለጫ ከዚህ ሕገወጥ ድርጊት ጋር ለማመሳሰል የሔዱበት ርቀት የአንድነት ምክንያት (unifying factor) ሆና የኖረችዋን ቤተ ክርስቲያን ለማፍረስ መንግሥትዎ ምን ያህል ቆርጦ እንደተነሣ የሚያስረዳ ነው። ሲጀመር በውጪ የተሾሙት ሊቃነ ጳጳሳት ሹመት ቀኖናዊ መሆን አለመሆን መመርመር የቤተ ክርስቲያን እንጂ የመንግሥት ሥልጣን አይደለም። አሁን ሾመናል፤ ተሹመናል የሚሉ አካላትንም ጉዳይ መርምሮ ቀኖናዊና አስተዳደራዊ ርምጃ መውሰድ የቤተ ክርስቲያን ሥልጣን ነው። መንግሥት ቀኖናዊ ጥሰት በፈጸሙ አካላት ላይ የተላለፈውን የቤተ ክርስቲያን ውሳኔ ከማስፈጸም ውጪ የውሳኔውን አግባብነት የመመርመርም ሆነ አቻ ምሳሌ በማቅረብ ሕገወጡ ድርጊት እንዲጸና የመጠየቅ/የማግባባት ሥልጣን የለውም። ለግንዛቤ ያህል ግን ውጪ ያሉት አባቶች የተሾሙት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ በፖለቲካ ጫና ተሰደው እንዲወጡ በተደረጉበት ወቅት ነው። ሹመታቸው የተፈጸመውም በቅዱስ ፓትርያርኩ ነው። በትግራይ ክልል የሚኖሩ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትን በተመለከተም አሁን እንደተፈጸመው ጳጳስ ሾመናል፤ ቅዱስ ሲኖዶስ አቋቁመናል የሚል መግለጫ ሲሰጡ አልታዩም።

ያልተካከለ ምሳሌ በመጥቀስ የሕገወጦቹን ዐሳብ ቃል በቃል ማቀንቀን የቃለ አቀባይነት ተግባር እንጂ አንድን ትልቅ ሀገር ከሚመራ መሪ አይጠበቅም። የተወገዙት ግለሰቦች “ሹመቱን ፈጽመን በእርቅ እና በድርድር አንድ እንሆናለን” በሚል ሒሳብ ያራምዱት የነበረው ዐሳብ ምንጩ ከየት እንደሆነም የሚያስረዳ ነው። ስለሆነም ከቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅናና ፈቃድ ውጭ፣ ቅዱስ ፓትርያርኩ በሌሉበት የተፈጸመውን ሕገ ወጥ ሹመት የፈጸሙና ያስፈጸሙ አካላትን ቤተ ክርስቲያን በእርቅና በድርድር እንድትቀበል መምሪያ አዘል ማስፈራሪያ መስጠታቸው ፈጽሞ በማያውቁትና በማያገባቸው ጉዳይ ገብቶ መፈትፈት ስለሆነ ቆም ብለው ሊያስቡበት ይገባል። ቤተ ክርስቲያን አውግዛ የለየቻቸውን አካላት በቀኖናዋ መሠረት በንስሐ እንጂ በድርድር ትመልስ ዘንድ ምድራዊት ተቋም አይደለችም። 


4.  በቋንቋ ስለመገልገል

ሌላው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ማብራሪያ የጠቀሱት መሠረታዊ ጉዳይ በቋንቋ ስለመገልገል ነው። ቤተ ክርስቲያን ያለችው ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ አይደለም። ባለችበት ቦታ ሁሉ በሕዝቡ ቋንቋ ታስተምራለች። ቋንቋ ገደብ ሆኖባት አያውቅም። ቤተ ክርስቲያን አንዲት እንደመሆኗ መጠን ቋንቋዬ ይህ ነው ብላ አታውቅም። አገሯ በሰማይ ቋንቋዋም ሰማያዊ ነው። ለቤተ ክርስቲያን ቋንቋዎች ከአገልግሎት መሣሪያነት ያለፈ ሚና የላቸውም። ምእመናንን በሁሉም ቋንቋዎች ለማስተማር ቤተ ክርስቲያን የአጭር ጊዜና የረጅም ጊዜ ሥልጠናዎችን በመስጠት ሰባክያንን እያፈራች እንዲሁም መጻሕፍትን በተለያዩ ቋንቋዎች በመተርጎምና በማስተርጎም ሁሉንም በሚሰማው ቋንቋ እያገለገለች ትገኛለች። በዚህ አንጻር ኃላፊነቷን ባትወጣ እንኳን ጠያቂዋ ሰማያዊው አምላክ እንጂ ምድራዊ ንጉሥ አይደለም። ሕዝቡ በሚሰማው ቋንቋ አገልግሎት መስጠት የቤተ ክርስቲያን ተልእኮዋ ቢሆንም መንግሥት ግን በዚህ ቋንቋ ስበኩ በዚህ ቋንቋ አትስበኩ ብሎ ማዘዝ አይችልም። እንደ ትምህርት ፖሊሲ የቤተ ክርስቲያንን የአገልግሎት ቋንቋ የመበየን ሥልጣን የለውም።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ “በቋንቋችን እንማር የሚለውን ጥያቄ ልናፍነው አንችልም” ያሉት ፈጽሞ ያለሥራቸው በመግባት የተደረገ ንግግር ነው። በዚህ ሳያቆሙ “በአማራ ክልል እና በትግራይ ክልል እንደሚደረገው በኦሮሚያ ክልልም በቋንቋቸው ሊማሩ ይገባል” በማለት ተናግረዋል። ይህ ፈጽሞ ከቤተ ክርስቲያን ጋር ውጊያ ላይ መሆናቸውን ከሚያስረዳ በስተቀር የሚሰጠው ትርጉም የለም። በአማራ ክልል ምእመናን በአማርኛ መማራቸው እውነት ቢሆንም በትግራይ ክልል በትግርኛ ትምህርት እንደሚሰጥ የተናገሩት ግን ያለማስረጃ ነው። የትና መቼ ቢባሉ መመለስ የሚችሉት አይደለም። በአገራችን ኢትዮጵያ ለብዙ ዘመናት የቤተ ክርስቲያን የአገልግሎት ቋንቋ ሆኖ ያገለገለውና እያገለገለ ያለው ግእዝ ቋንቋ ነው። አሁንም በሁሉም አካባቢዎች ቅዳሴ የሚቀደሰው በግእዝ ነው፤ ማሕሌት የሚቆመው በግእዝ ነው። እየተባለ ያለው ነገር እውነት ነው ቢባል እንኳን መምህራኑ ሳባክያነ ወንጌል እንጂ ጳጳሳት አይደሉም። በቋንቋ ማስተማርን መፍታት የሚቻለው ሰባክያንን በማብቃት እንጂ ሕገወጥ ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት በመፈጸም አይደለም። በቋንቋ ማስተማርና ሕገወጦቹ ቡድኖች የፈጸሙት ሕገ ወጥ ሢመተ ጵጵስናም ፈጽሞ ግንኙነት የለውም። ሁለቱም ጋ እውነት አለ በማለት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጠቀሱት የሕገወጦቹ እውነት ምን እንደሆነ ግልጽ አይደለም።  ይህ አገላለጽ የተፈጸመውን ሃይማኖታዊ እና ቀኖናዊ ጥሰት በቋንቋ እናስተምር ብለው የጠየቁ አካላት በቋንቋ አታስተምሩም ተብለው የተከለከሉ በማስመሰል የቀረበ ስለሆነ ፈጽሞ አግባብነት የሌለው ነው፡፡ 

ቤተ ክርስቲያን ልጆቿ ብቻ ሳይሆኑ ያላመኑበትንም ለማሳመን በተለያዩ በሀገረ ውስጥና በውጭ ዓለማት ሳይቀር አገልግሎቷን በቋንቋ ተደራሽ ለማድረግ በሕገ ቤተ ክርስቲያን ጭምር በመደንገግ እየሠራችበት የምትገኝ መሆኗ እየታወቀ የሕገ ወጡን ቡድኑን ፍቅረ ሢመተ ጵጵስና በቋንቋ ከመገልገል ጋር በማዳበል የቀረበው ስሑት ግላጼ ሊታረቅ የሚገባው ነው። በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በቋንቋ የማስተማር ዓላማው ነፍሳትን በሚረዱት ቋንቋ ከእግዚአሔር ጋር ለማገናኘትና ለመንግሥተ ሰማያት የበቁ ለማድረግ እንጂ ቋንቋን ማሳደግ አይደለም። የቋንቋ ልማት የመንግሥት ኃላፊነት መሆኑን ከዘነጉት ልናሳስብዎ እንወዳለን። ቤተ ክርስቲያን ግን በየትኛውም ክልል ቢኖሩ ቋንቋውን መስማት እስከቻሉ ድረስ በአንድ ቋንቋ ከማስተማር የሚከለክላት ነገር የለም። ቋንቋውን እስካልሰሙ ድረስ ደግሞ በሚሰሙት ቋንቋ ማስተማር ከአምላኳ የተረከበችው መንፈሳዊ ኃላፊነቷ ነው። መንግሥት በሚሰሙት ቋንቋ ካልሰበካችሁ ብሎ “በብሔር ተዋጽዖ” የራሱን ጳጳሳት የሚሾምበት አግባብ ሊኖር አይገባም። በዚህ ረገድ ክፍተቶች መኖራቸው ቢታመንም ዘውግን መሠረት በማድረግ የተፈጸመ አድሎ እንዳለ በማስመሰል የቀረበው ግን ፈጽሞ እውነትነት የለውም። “ሌላው ክልል እንደሚደረገው እኛም ክልል ያሉ ኦርቶዶክሳውያን የግድ በራሳቸው ቋንቋ መማር አለባቸው” የሚለው መመሪያ አዘል ማብራሪያም ኩሸትና ጣልቃገብነት መሆኑን ማስገንዘብ እንወዳለን።

ቤተ ክርስቲያን ሁሉም በሚሰማው ቋንቋ ለማስተማር የራሷን መርሐ ግብር ዘርግታና ስልት ነድፋ እየሠራች ነው። ሕገወጥ ሢመት የፈጸሙትም ሆኑ በሕገወጥ መንገድ ተሹመናል የሚሉት አካላትም በተለያዩ ቋንቋዎች ማስተማር የሚችሉ ቤተ ክርስቲያን ለዘመናት የደከመችባቸውና ከዚህ መዓርግ ያደረሰቻቸው እንጂ በተአምር የተገኙ አይደሉም። ደግሞስ እነ አራርሳ ጎንፋ ከመቼ ወዲህ ነው ለኦሮሞ ሕዝብ በቋንቋው መማር የሚገዳቸው የሆኑት? አሜሪካ ለትምህርት ብለው ወጥተው ትምህርታቸውን ከጨረሱ በኋላ ነገሌ ቦረና ሀገረ ስብከት ተመድበው እንዲያገለግሉ በቅዱስ ሲኖዶስ ከአምስት ጊዜ በላይ ጥሪ ሲደረግላቸው አልመጣም ብለው በእምቢተኝነት የቀሩ አይደሉምን? ታዲያ ዛሬ በምን ምክንያት ነው በቋንቋ መማርን እንደተከለከሉ በማስመሰል በእርስዎ በኩል ለመናገር የፈለጉት? ጠቅላይ ሚኒስትሩ የውጉዛኑን ድርጊት ሕጋዊነት ያለው በማስመሰል ለማጽደቅና ለቡድኑ ዕውቅና ለመስጠት የሔዱበት ርቀት በእጅጉ የሚደንቅ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ለተፈጸመው ሃይማኖታዊና ቀኖናዊ ጥሰት የወሰነችውን ሲኖዶሳዊ ውሳኔ ቋንቋን መሠረት በማድረግ የተወሰነ አድሏዊ ውሳኔ በማስመሰል የቀረበው አገላለጽ ቤተ ክርስቲያንን የማይወክልና ዓላማዋን የረሳ ነው፡፡ 

ማንም ጣልቃ እንዳይገባ በማለት የዛቱት ሕገወጦችንም በመደገፍ አንጻር ከሆነ እባክዎ እርስዎም እጅዎትን ይሰብስቡልን። ንግግርዎ የመሪነት ጥበብ እንደጎደለዎት፣ አማካሪም እንደሌለዎት የሚያረጋግጥ ነው። እርስዎ ወይም አማካሪዎችዎ ስለ ቤተ ክርስቲያን ያላችሁ ግንዛቤ የተሳሳተ እንደሆነ ከንግግርዎ መረዳት ይቻላል። ቤተ ክህነትን ከቤተ ክርስቲያን የለዩ እንኳን አይመስልም። ቤተ ክርስቲያን ራሷ ክርስቶስ የሆነላት በምድር ያሉ የክርስቲያኖች በሰማይ ያሉ የቅዱሳን ኅብረትና አንድነት ናት። እየተዋጉ ያሉት ምድራዊ ተቋም ጋር ሳይሆን ከእነዚህ አካላት ጋር ነው። እናም እፍ ሲባል እንደሚበራ፣ ትፍ ሲባል እንደሚጠፋ እሳት መሆንዎን ረስተው በዚህ ልክ ቤተ ክርስቲያንን ለመገዳደር መነሣትዎ በእውነቱ መከራን እንጂ ዕድሜን አያረዝምም። ለማንኛውም ከፎከረ ቀርቶ ከወረወረ የሚያድን አምላክ እንዳለን በመተማመን ተጋድሏችንን እንደጀመርን ስናበሥርዎ በፍጹም ደስታ ነው፡፡ ምናልባት ባንክና ታንክ በእጅዎ ስላለ ለጊዜው በሥጋ ሊያስገድሉን ይችላሉ። ነገር ግን ሞት ከምትታየዋ ቤተ ክርስቲያን ወደማትታየዋ ቤተ ክርስቲያን የሚደረግ ጉዞ እንጂ የሕይወት መጨረሻ እዳልሆነ ስለምናምን ሞትን ልንፈራው አንችልም። አሸናፊውንም በቅርቡ የምናየው ይሆናል። 


እስከዚያው በድጋሚ፡-

  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳለፈው ውሳኔ ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ከእርስዎ ጀምሮ በመሸኛ ደብዳቤ በአድራሻ የተላከ ስለሆነ በውሳኔው መሠረት ሰላምና ጸጥታ የማስከበር ኃላፊነትዎን በአግባቡ እንዲወጡ ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡
  • ሃይማኖታዊና ቀኖናዊ ጥሰት በመፈጸም በሕገ ወጥ ሢመተ ጵጵስና ላይ የተሳተፉ አካላት በቤተ ክርስቲያን የተወገዙና ከቤተ ክርስቲያን የተለዩ በመሆናቸው በተለያዩ አኅጉረ ስብከት እየፈጸሙት ያሉት ሕገወጥ ወረራና ሁከት እንዲቆም በድጋሚ እንጠይቃለን፡፡
  • ቤተ ክርስቲያን የወሰነችውን ሲኖዶሳዊ ውሳኔ በዘር፣ በቋንቋና በፖለቲካ ምዛሬ በመተርጎም በእርስዎ ዘንድ የተያዘው አቋም ስሑት መሆኑን እየገለጽን በድርድርና በእርቅ የሚፈታ ቀላል ጉዳይ ተደርጎ መወሰዱ የቤተ ክርስቲያንን ቀኖናዊ ሥርዓት ካለመረዳት የመነጨ ብቻ ሳይሆን በውስጥ ጉዳይዋም ጣልቃ እንደመግባት ስለሚቆጠር ከዚህ አካሔድዎ እንዲታቀቡ እናሳውቃለን፡፡  
  • በሕገወጥ መንገድ ሢመተ ጵጵስና የሾሙና የተሾሙ አካላትን ቤተ ክርስቲያን የምትቀበልበት የራሷ ሃማኖታዊና ቀኖናዊ ሥርዓት ያላት በመሆኑ እና ይህንም ባስተላለፈቸው ውሳኔ በግልጽ ያስቀመጠች በመሆኑ በድርጊታቸው ተጸጽተው በንስሐ ሲመለሱ ብቻ የምትቀበላቸው ከሚሆን በስተቀር በፖለቲካዊ ጫና ሊፈጸም የሚችል ድርድር እንደሌለ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡


ይቆየን!

Wednesday, February 1, 2023

በቋንቋ መገልገልን እንደፖለቲካ መሳርያ

 

አቶ ዋስይሁን

         አቶ ዋስይሁን እና ጀሌዎቹ የፖለቲካ ስካራቸውን ለማብረድ የተጠቀሙት ስልት “ቅዳሴ በኦሮምኛ ስለማይቀደስ ሕዝቡ እምነቱን ቀየረ።” የሚል የአዛኝ ቅቤ አንጓችነትን አካኸኼድ ነበረ። በምዕራብ ወለጋ በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ወንጌል ማስተማር የተጀመረው ኢሀዴግ ሀገሪቱን በተቆጣጠረበት ማግስት ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህ ሲባል ከዚያ በፊት ሲሰጥ አልነበረም ማለት ሳይሆን ተጠናክሮ የቀጠለው ለማለት እንደሆነ ግንዛቤ ሊያዝበት ይገባል።
ምክንያቱም እነ ቀሲስ ገመቹ፣መጋቤ ሃይማኖት ይኄይስ ሞገስ፣ቀሲስ ዋስይሁን፣ኦርዶፋ፣ቄስ በዳሳ እና ሌሎችም በየገጠር አድባራቱ እየዞሩ ሲያስተምሩ የኖሩት በአፋን ኦሮሞ እንደሆነ እማኞች የሚመሰክሩት እውነት ነውና። የአፋን ኦሮሞ ቋንቋ የማይችሉትም እያስተረጎሙ በትርጁማን ያስተምሩ እንደነበረ ይህንን ጽሑፍ ለማዘጋጀት ባደረግነው ጥናት ለማረጋገጥ ችለናል።

ቤተክርስቲያን በልዩ ልዩ  ቋንቋዎች የምታስተምረው ሰዎችን ለማስደሰት ሳይሆን አምላካዊ ትእዛዝ መፈጸም ተልዕኮዋ ስለሆነ ነው።  “ካልሰሙ እንዴት ያምናሉ?ካለመኑስ እንዴት ይጸድቃሉ?” ጌታም ለቅዱሳን ሐዋርያት አባቶቻችን ከሚያውቁት አንድ ቋንቋ ተጨማሪ 71 ቋንቋዎችን የገለጸላቸው በቋንቋ ምክንያት ወንጌል ከመስፋፋት እንዳይገታ መሆኑን ጠንቅቃ ትረዳለች። በርግጥ የቀደሙት አባቶቻችን መናፍቃኑ በሠሩት መጠን ጠንክረው ሰርተዋል ለማለት ያስቸግራል።
የሆነው ሆኖ በእነ ዋስይሁን አመለካከት ክርስቲያኖችን በሃይማኖታቸው ለማጽናትም ሆነ ወደ ቀደመች እምነታቸው እንዲመለሱ ለማድረግ የሚያግዘው ስብከተ ወንጌል እንጂ ቅዳሴ በኦሮምኛ መቀደሱ እንዳልሆነ መረዳት ጥናት አያሻውም። ምክንያቱም የቅዳሴን ትርጉም የማያውቀው የኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪ ብቻ ሳይሆን ግዕዝን ያልተማረ የየትኛውም ብሔር ተወላጅ እንደሆነ እሙን ነውና። ሌላው ቅዳሴ የጸሎት አገልግሎት ነው። ሰብከተ ወንጌል የቅዳሴው አንድ አካል ሲሆን ሲሰጥ የኖረው በኦሮምኛ ቋንቋ እንደሆነ ከዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ በላይ እነ ቄስ በጻሳ ህያው ምስክር ናቸው።
ትግላቸው ስለሰው ልጅ መዳን በማሰብ በፍቅርና በትህትና ሳይሆን በትዕቢትና በመናቅ ቢሆንም ብጹዕ አቡነ ሔኖክ ቅዳሴ ወደ አፋን ኦሮሞ እንዲተረጎም ለቅዱስ ሲኖዶስ አቅርበው ሲኖዶስም ያለምንም ማንገራገር ተቀብሎ ከፍተኛ ወጪ ወጥቶበት ታትሞ ተሰራጭቶ በአገልግሎት ላይ እንዳለ እንኳንስና ኦርቶዶክሳውያን ሙስሊሞች እና ፕሮቴስታንቶች ይመሰክራሉ። በጣም የሚገርመው ግን በኦሮሚያ ውስጥ ያሉ የእስልምና እምነት ተከታዮች ትምህርታቸውም ሆነ የጸሎት ሥርአታቸውን የሚከውኑት በአረብኛ ሲሆን እነሱ ላይ የተነሳ አብዮት ግን የለም። ታዲያ በኦርቶዶክስ ላይ የበረቱት ለምንድን ነው? የሚል ጥያቄ እንድናነሳ ግድ ይለናል።
ቅዳሴ ወደ ኦሮምኛ መተርጎሙ እነዚህን አካላት አላስደሰታቸውም። ምክንያቱም ታሪክንም የመሻማት አባዜ የተጠናወታቸው ስለሆኑ። በእነሱ ያልተወጠወጠ ወጥ ስለማይጣፍጥ! ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲሉ የቀድሞው የደቡብ ምዕራብ ሻዋ ሀ/ስብከት ጳጳስ የነበሩት ሳዊሮስ በምን ሒሳብ የቋንቋው ጠበቃ ሊሆኑ እንደቻሉ ሳስበው እጅግ በጣም ይደንቀኛል። ምክንያቱም በሀ/ስብከታቸው በሁከት ፈጣሪነታቸው የሚታወቁ፣ከክፉ ሥራቸውም የተነሳ ስጋት ስለሚያድርባቸው/ሀጢያተኛን ማንም ሳያሳድደው ሥራው ያሳድደዋል እንዲባል/ አንድ ቀን ሀገረስብከታቸው አድረው የማያውቁ፣ሀገረ ስብከቱ ላይም እዚህ ግባ የሚባል አገልግሎት ያልፈጸሙ እንደሆኑ የወሊሶ ሕዝበ ምዕመን ህያው ምስክር ነው። ይኽንን ሳስብ “መጽሐፍ ምናምንቴ ከፍከፍ ያለበት ዘመን” ያለውን ያስታውሰኛል።
ጉዳዩ በግልጽ ፖለቲካዊ ፍላጎት ያለበት መሆኑን እንደነዚህ ያሉ ከእውቀት፣ከአባታዊ ሞገስና ክብር የተራቆቱ፣እግዚአብሔር ለማይረባ አዕምሮ አሳልፎ ከሰጣቸው ግለሰቦችን በመጠቀም ሴረኛው መንግስት ሰሞኑን ምዕራብ ወለጋ ላይ የሠራውን ማየት በቂ ነው። እነዚህ ሰዎች ሃይማኖተኞች አለመሆናቸውን በውል እንረዳለን። ምክንያቱም ወገኞቻችን በሃይማኖታቸው ምክንያት ሻሸመኔላይ፣ምዕራብ ሸዋ ላይ፣ሰሜን ሸዋ ላይ እና ሌሎችም የኦሮሚያ አካባቢዎች ላይ እንደበግ ሲታረዱ፣አጥብያ አብያተ ክርስቲያናት እንደችቦ ሲነዱ ቃል አልተነፈሱም። ከዚያ ይልቅ ጎንደር ላይ በተፈጸመው ግድያ የሙስሎሞች ጠበቃ ሆነው ሲሞግቱ አስተውለናቸዋል። ጫካ አለ የሚሉት ኦነግም ቀኝ እጃቸው ስለሆነ በነገር ሁሉ ይደግፉታል እንጂ ምን ሲሆን ይቃወሙታል?። እንቀጥላለን።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ሲገመገም

 



ትናነት ጥር 23 2015 ዓ/ም በሰላምና ሃይማኖታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ጠቅላይ ሚንስትሩ የሰጡት መግለጫ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ የተደረገው ሕገወጥ ድርጊት ዓላማው ምን እንደሆን በግልጽ የሚያሳይ ማብራሪያ ነው። አንዳንድ ያነሱትን ሃሳቦች አሁን መንግስትዎ እያደረገ ካለው ድርጊት ጋር አያይዞ መገምገም የማብራሪያውን ዓላማ ለማወቅ ይረዳል።

1.       ፀረ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ትርክት ላይ የተመሠረተ እና ይህንኑ የሚያጠናክር ነው።

1.1.     ጠቅላይ ሚንስትሩ በንግግራቸው ከቤተ ክርስቲያኒቱ ሕግ ውጭ የተፈጸመውን የጳጳሳት ሹመት ፈጻሚዎቹ እንዳሉት በኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄ መሠረት የተደረገ ነው ሲሉ የዓላማ መስማማት እንዳላቸው ከማሳየትም በላይ፣ ድርጊቱን ሕጋዊ ለማስመሰል ሞክረዋል፡፡

1.2.    በተለያዩ የቀድሞ መንግስታት ጳጳሳት እና በተለይም ፓትርያርኮች በነገሥታቱ፣ በኋላም ከዛ በኃላ በተነሱ መንግስታት ምርጫ እና ሹመት ይሾሙ እንደነበር በመጥቀስ፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ ምንም ዓይነት የሹመት ሥርዓት እንዳልነበራት፣ እንደውም ከዚህ በፊት የታየውን የመንግስታት ጣልቃ ገብነት አጽድቀው፣ የቅ/ሲኖዶሱን ምላሽ ከብሔር ፖለቲካ ጋር ለማያያዝ መሞከራቸው፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ የሁሉ እንዳልሆነች የሚነሳውን የሐሰት ትርክት የሚያጠናክር ነው፡፡

1.3.    በትግራይ ያሉ አባቶች በራሳቸው ቋንቋ እየተገለገሉ ከቤተ ክርስቲያን ወጥተናል ሲሉ ምንም አይነት ምላሽ ሳይሰጥ፣ በኦሮሞ ለሚነሳ ጥያቄ ይሄ ሁሉ ግርግር በማለት፣ ጉዳዩ በተለየ ሁኔታ ለኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄ ምንም ምላሽ ላለመስጠት የተደረገ አስመስለው አቅርበዋል፡፡

1.4.    ክቡር ጠቅላይ ሚነስትር ለሁለት ሺህ ዓመታት ሕዝቡን በቁንቋ እና በዘር ሳትከፋፍል አጣምራ የኖረች ቤተ ክርስቲያንን የዘር ፖለቲካ ለወለደው ችግር ምክንያት አድርጎ ማቅረብ ቤተ ክርሲትያኗን ለማጥፋት የሃሰት ትርክት ከሚያስተጋቡ አካላት ተልይቶ አይታይም። ይልቅስ አሁን በቤተ ክርስቲያን የተፈጠረው ችግር መንግስት ለሚመራው ዘር ተኮር ፖለቲካ የውድቀት ማሳየ መሆኑን ነው የሚያስገነዝበው። ቢያንስ መንግስት የእምነት ተቋማትን ከዚህ ለመጠበቅ ተገቢውን አስተዋጽኦ ማድረግ ሲገባው በአንጻሩ በዚሀ ጥቂት ቀናት ውስጥ እንደሚታየው የጠቅላይ ሚንስትሩ መንግስት የችግሩ ፈጣሪ እና መሪ እንደሆነ የሚያሳይ ነው።

2.     መረጃዎችን በተሳሳተ መልክ በማቅረብ የተሳሳተ ግንዛቤ እንዲኖር ማድረግ

1.1.     ከዚህ በፊት የነበረውን የቤተክርስቲያን አባቶች ልዩነትን ለማጥበብ ያደረጉትን ውለታ ጠቅሰው በሚያብራሩበት ክፍል፣ በውጭ የነበሩ አዳዲስ ጳጳሳት ከጵጵስና በፊት ባለው መዓረግ እንኪደርሱ በቤተ ክርስቲያን የነበሩ በመሆናቸው በእርቁ ከነባሮቹ ጋር አብረው የሲኖዶስ አባል እንዲሆኑ መደረጉን አብራርተዋል፡፡ ልዩነቱን በትንሹ ለማንሳት ግን፣ የውጪ አገሩ ሲመት የተፈጸመው በፓትርያርኩ በበጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ መሪነት እንጂ ራሱን ፓትርያርክ አድርጎ በሾመ ሕገወጥ አካል አይደለም።

1.2.    “አሿሿም ላይ አድሎ አለ፣ ህገመንግስታዊ መብታችን አልተጠበቀም የሚሉ ጥያቄች መጡ፣ መከርን አልተደመጥንም፡፡ ኦሮሚያ ውስጥ በቋንቋ ልማር ሲል አይ አያስፈልግህም ልንል አልችልም” በማለት ቤተክርስቲያኒቱ በኦሮምኛም ሆነ በሌሎች ቋንቋዎች አገልግሎት እየሰጠች እንዳልሆነ እና ይህንኑ አገልግሎት ለማሳደግ እንዳልተዘጋጀች በማስመሰል ለማብራራት ሞክረዋል፡፡ ሁለቱ ክስተቶች በምንም የማይገናኙ መሆናቸው ግልጽ በሆነበት ሁኔታ ሆን ብሎ የተሳሳተ መረጃን በመስጠት፣ በተለይም በኦሮሞ ተወላጆች የቀረበ ጥያቄ ሲሆን የተለየ ምልሽ እንደተሰጠው በማስመሰል የብሔር መልክ ለመስጠት እና ቤት ክርስቲያኗን ለመውቀስ ሞክረዋል፡፡

1.3.    ቅዱስ ሲኖዶስ ሕገ ወጥ ሢመት የፈጸሙትን እና የተሳተፉትን አካላት ማውገዙን ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን አንጻር ሳይሆን ሌላ መልክ ለማስያዝ ሌላው ያነሱት ሃሳብ፣ በሰሜኑ ክፍል ጦርነቱን ተከትሎ በትግራይ ያሉ ጳጳሳት ከቤተ ክርስቲያን ተለይተናል ሲሉ ቅዱስ ሲኖዶስም ሆነ ሌሎች የቤተ ክርስቲያን አካላት ምንም ነገር እንዳልተናገሩ ገልጸዋል። ነገሩ “It is like comparing apples and oranges.” እንደሚባለው የፈረንጆች ብሂል ነው። ምክንያቱም፡

2.1.1.    “ተለይትናል” አሉ እንጂ ፓትርያርክም፣ ጳጳሳትም አልሾሙም። የኑፋቄ ትምህርት ካልሆነ ቤተ ክርስቲያን ሰውን በሕገወጥ ድርጊት እንጂ በንግግር ምክንያት ብቻ አታወግዝም።

2.1.2.   በጦርነቱ በትግራይ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የተፈጸመው እልቂት ገና ተነግሮ አላለቅም። በብሶት የተነገረን እና የተፈጸመን ተግባር የመከፋፈል ዓላማ ይዘው ከተነሱ ሐሰተኞች ጋር ማወዳደር አገሪቱ ውስጥ የተፈጠረውን ቀውስ ገና አልተረዱትም ያሰኛል።

2.1.3.   በሰሜኑ ያሉ አባቶች ‘ተለይተናል’ ሊሉ የሚችሉበት ፖለቲካዊ ጫና ሊኖር እንደሚችል እየታወቀ እና ችግሩ ከሰላም መስፈን ጋር በራሱ እንዲሚፈታ እየታወቀ ‘ነጻነት’ ባለበት አገር ሕገ ወጥ፣ ሕዝብን እና አገርን የሚከፋፍል ተግባር ከፈጸሙ አካላት ጋር ማወዳደር ተገቢ አይደለም።

2.2.   ከዚሁ ጋር አያይዘው ይህ መንግስት ለኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከአባቶች እርቀ ሰላም ጀምሮ የተለየ ድጋፍ ሲያደርገ መቆየቱነ ገልጸዋል። ለዚህም አንዱ ማሳያ ያደረጉት መንግስታቸው በአዲስ አበባ  መስተዳድር ካሏት ይዞታዎች ለተወሰኑቱ ብቻ ያደረገውን ሕጋዊ ይዞታ የማረጋገጥ ተግባር፣  ለሌሎች የእምነት ተቋማት ከተደረገው አዳዲስ የመሬት ስጦታ ጋር በማነጻጸር የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከሌሎች የእምነት ተቋማት በበለጠ ሰፊ የመሬት ሥጦታ እንዳገኘች አድርገው ማቅረባቸው ነው፡፡ ይህ መረጃ ትክክል ቢሆን እንኳ፣ ከአዲስ አበባ ውጪ ያለውን የቤተ ክርስቲያኗን የመሬት ይዞታ መንጠቅ፣ የኦርቶዶክሳውያንን መፈናቀል እና መገደል ሳያነሱ ማለፍ እውነት የሚመስል የሃሰት ትርክት ማናፈስ ነው።

3.     ህጋዊ ሰውነት ያላትን የሃይማኖት ተቋም ከሕጓ ውጭ ራሳቸውን የሾሙ አካላት ጋር በእኩል ማስቀመጥ

3.1.    ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው ሕጋዊ የሆነውን የቤተ ክርስቲያኗን ቅዱስ ሲኖዶስ እና በሕገ ወጥ መልኩ የተሿሿሙትን ግለሰቦች/ቡድን እንደ እኩል ሕጋዊ አካላት ሲያወዳድሩ ይሰማሉ። ይህም፡

3.1.1.    ጋዊ ለሆኑ ነባር ተቋማት ሕጋዊ መሠረትን የናደ ነው፣

3.1.2.   ቅዱስ ሲኖዶስ ከዚህ ሕገ ወጥ አካል ጋር እንዲደራደር ጫና ለማሳደር የጠቅላይ ሚንስትሩ መንግስት እየሄደበት ላለው ግልጽ የጣልቃ ገብነት እንቅስቃሴ ማሳያ ነው።

3.1.3.   ዛሬ ሁለቱም ችግራቸውን በድርድር የሚለው መንደርደሪያ፣ ይሄው ሕገ ወጥ ቡድን በቀጣይም በየአህጉረ ስብከቱ የሚያከናውናቸውን ሕገ ወጥ የቤተ ክርስቲያኒቱ አደረጃጀቶች ዘረፋ እና ወረራ፣ “ሁለቱም አካላት” ተስማምተው ይፍቱት በሚል ሕጋዊ የሆነ ምላሽ ከመስጠት እንዲቆጠቡ ለማመቻቸት ነው፡፡

3.1.4.  እንደውም ድርድሩ ሕገ ወጥ ቡድኑ ያደረገውን ሥርዓት አልባ ሹመት ቅዱስ ሲኖዶሱ እንዲቀበል በሚመስል መልኩ ቀደም ብሎ በነበረው የአባቶች እርቀ ሰላም በውጪ የተሾሙትን ጳጳሳት ቅዱስ ሲኖዶስ እንደተቀበለ አንስተዋል። ነገሩ እንደተባለው“It is like comparing apples and oranges.” ነው።

4.     ፍትህ እና ሕጋዊ ከለላ መንፈግ፣ እና ወደፊትም ለዚህ እንዳልተዘጋጁ የሚያመለክት ንግግር ነው።

4.1.    እንደተለመደው አገር ውስጥ ለሚፈጠር ችግር በሙሉ መንግስት ምንም ዓይነት ተጥያቂነት እንደሌለው በተለመደ መልኩ ገልጸዋል፡፡ ራስን መግምገምና ስህተቶችን ማመን ችግርን ለመፍታት ፍላጎት ካለው መንግስታዊ ተቋም የሚጠበቅ ነው።

4.2.   ጠቅላይ ሚኒስትሩ ‘በሁለቱ አካላት’ መሃል ጣልቃ እንደማይገባ አስረግጠው ተናገረዋል። ነገር ግን በመግለጫቸው ያነሷቸው ሃሳቦች በሙሉ ሕገ ወጥ በሆነ መልኩ የተሿሿሙትን አካላት እንደምክንያት ከሚያቀርቧቸው ጉዳዮች እና ትርክቶች ጋር የተስማማ መሆኑ በራሱ መንግስታቸው ያለውን ተሳትፎ በግልጽ የሚያሳይ ነው፡፡ ይህ ከእውነት የራቀ፣ ዓይን ያወጣ እና የሚያስገምት ሐሰት ነው። ለቤተ ክህነት የነበረውን ጥበቃ ያነሳ፣ ጳጳሳትን ጨምሮ እያንገላታ እና እያሠረ ያለው፣ የቤተ ክርስቲያኗን ንብረት የሚያሰብረው ማነው? ሌላ የማናውቀው መንግስት አለ እንዴ? የሚያሰኝ ነው፡፡

4.3.   ጉዳዩ ግን ከላይ እንደተመለከትነው፣ ይሄው ሕገ ወጥ ቡድን በየክልል መንግስታት ጥበቃ እና ድጋፍ በቀጣይም በየአህጉረ ስብከቱ ከአጥቢያ ቤተክርስቲያናት ጀምሮ፣ ወረዳ ቤተ ክህነት እስከ አህጉረ ስብከት ድረስ ያሉ የቤተ ክርስቲያኒቷን አደረጃጀቶች ሁሉ እንደፈለጉ፣ በጉልበት የመውሰድ ተግባር፣   ከለላ ለመስጠት እና ቤተክርስቲያኒቱ ለምታነሳው የፍትህ ጥያቄ “ሁሉቱም ተስማምተው ይፍቱት በሚል ኢ_ፍትሃዊ አካሄድ ለማለፍ እንዲያስችላቸው መሆኑ ግልጽ ነው፡፡

4.4.   ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጀምሮ አባቶች እና የቤተ ክርስቲያን አካላት መንግስት ሕግ የማስከበር ኃላፊነቱን እንዲወጣ እያሉ የሚማጸኑት እኮ ሀገሪቱ ፍትሐዊ  መንግስት አላት ብለው ነው። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፣ እስኪ ወደ አገረ ስብከታቸው እንዳይገቡ እና በምእመናን ገንዘብ በጅማ ያስገነቡትን ቤተ ክርስቲያን እንዳይመርቁ የተከለከሉተን፣ ከጂማ ኤርፖርት ታስረው ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ የተገደዱትን አረጋዊውን አባት በፁዕ አቡነ እስጢፋኖስን ይጠይቁ።

5.     ስለፍትህ የሚደረገን የኦርቶዶክሳዊያንን እንቅስቃሴ ሁሉ ከሰላም ማናጋት እና ብሎም መንግስትን በኃይል እስከመገልበጥ የሚቆጠር እንደሆነ መግለጻቸው፣

5.1.    ይህን ችግር አስመልቶ ኦርቶዶክሳውያን፣ በዘር እና ቋንቋ ሳይለዩ ከሁሉም አቅጣጫ እያሰሙ ያሉትን ድምጽ ለመንግስት ለውጥ የሚደረግ እነቅስቃሴ ለማስመሰል እና እንዲህ ዓይነት እንቅስቃሴን የሚቆጣጠር አቅም እንዳላቸው በማስፈራሪያ መልክ ተናግረዋል። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፣ “ሺ ዓመት ንገሱ፣ እጅዎን ግን ከቤተ ክርስቲያን ያንሱ” ነው የቤተ ክርስቲያን፣ የአባቶች እና የምእመናን ድምጽ።

5.2.   አባቶች እና የቤተ ክርስቲያ አካላት የመንግስት ጣልቃ ገብነት አገሪቱን ወዳልተፈለገ ቀውስ ሊያደርሳት ይቻላል የሚል ሥጋታቸውን የሚገልጹት፣  አሁን እንደምናየው መንግስት የምእመናን ድምጽ ለማፈን እና ፍላጎቱን ለማስፈጸም ኃይል እንደሚጠቀም በመገንዘብ ነው። ነገር ግን መስዋዕትነት ቢያስከፍልም በቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሰ ያለው በደል በዝምታ የሚታለፍ እንዳልሆነ ግልጽ ነው። ለዚህ ነው ምእመናነ በየቦታው “የምንሞትለት ሃይማኖት እንጂ የምንሞትለት ብሔር የለንም” የሚል መፈክር ይዘው የሚታዩት። ለምዕመናን ድምጽ መንግስት ጠመንጃ ሳይሆን ጆሮውን ከሰጠ ችግሮቹን መፍታት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር እንዳሉት ‘ቀላል’ ባይሆንም የሰላም መንገድ ከፋች ነው።

6.     ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት ቀላል እንደሆነ መናገራቸው

6.1.     አገሪቱን አሁን ላለችበት ቀውስ ከዳረጉ ነገሮች አንዱ ግዙፍ ችግሮችን እንደ ኢምንት ከመቁጠር የመነጨ ነው። ሕዝቡን በሃይማኖት እና በማኅበራዊ ኑሮ አዛምዳ ያኖረችን ቤተ ክርስቲያን በዘር እና በቋንቁ ለመክፈል የሚደረግን ድርጊት ‘ቀላል’ ነው ብሎ ማለፍ ወይ ችግሩን አለመረዳት ወይም ችግሩ እንዲፈታ ያለውን የፍላጎት ማነስ ያመለክታል። ወይም የመንግስትን በችግሩ ያለውን ቀጥተኛ ተሳትፎ እና ለሕገ ወጥ አካላት የሚሰጠውን ድጋፍ ለመሸፈን የሚደረግ ሙከራ ነው።

7.     በተለያዩ የእምነት ተቋማት ለሚፈጠር ችግር የተቋማቱ ብቸኛ ችግር አድርጎ የመንግስትን ጣልቃገብነት መካድ

7.1.    የእምነት ተቋማት ችግር ውስጥ እንዳይገቡ ክፖለቲካ፣ ከሌብነት እና ከዘር ነጻ መሆን እንዳለባቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል። ጥሩ ምክር ነው። መንግስት እጁን ከቤተ ክርስቲያን ላይ ካነሳ ሁሉም ችግር ይቀረፋል። ሦስቱንም ችግሮ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በተለያየ ዘማናት ያስገባወ መንግስት ነው። የቀድሞዎቹ ስላለፈ አሁን የጠቅላይ ሚንስትሩን መንግስት ሚና ማሳያው

7.1.1.    በጠቅላይ ሚንስትሩ የሚደገፉ አንዳንድ የብልጽና ፓስተሮች ቤተ ክርስቲያኗን የኋላ ቀርነት ምክንያት አድርገው ለአገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ቀውስ ተጠያቂ እንደሆነች ሲናገሩ በዝምታ ማለፍ

7.1.2.   የቤተ ክርስቲያኗን ሕጋዊ ኅልውና ከኅገወጥ አካል ጋር አስተካክሎ ማየት

7.1.3.   ቀደም ብሎ እንደተገለጸው በፖለቲካው መስመር ቤተ ክርስቲያንን በዘር ለመከፋፈል የሚሞክሩ ሕገ ወጥ አካላትን በግልጽ መደገፍ

7.1.4.  ዛሬ ባደረጉት ንግግር ጭምር ቤተ ክርስቲያን የሰዎችን በቋንቋቸው የመማር መብት እንደምትገፍ የሚያስመስል ጠባ አጫሪ ንግግር ማድረግ ናቸው።

ማጠቃለያ

የጠቅላይ ሚንስትሩ ንግግር በጥቅሉ ችግር ፈቺ ሳይሆን አሁን በተፈጠረው ችግር ላይ ቤንዚን ያርከፈከፈ እና ከተጠያቂነት የማያድን ንግግር ነው። ለችግሩ ሰላማዊ መፍትሔ እንዲመጣ መንግስት ጣልቃ ገብነቱን ትቶ

1.      የቅድስ ቤተ ክርስቲያኗን ሕጋዊ ኅልውና ተቀብሎ ሕጋዊ መብቷን ማስከበር

2.     በቤተ ክርስቲያኗ እና በአገልጋዮች ላይ የሚደርሰውን መዋቅራዊ ጥቃት ማስቆም

3.     የዜጎችን ሕገ መንግስታዊ ሃስብን በነጻነት የመግለጽ መብት ማክበር እና ለሚያነሱት ጥያቆ ጆሮ መስጠት አገር ከሚመራ መንግስት እና መሪ የሚጠበቅ ተግባር ነው።

Monday, January 30, 2023

የሕገ ወጥ ሲመተ ጵጵስና መሐንዲሶች (ካባለፈው የቀጠለ)


አቶ ዋሲሁን አመኑ ቤተክርስቲያንን ለመክፈል ሀገርን ለማፍረስ እንቅልፍ አጥቶ የሚሠራ ግለሰብ ነው። ይህንን ሰው ከመጥላት ሳይሆን በተጨባጭ ከሚሠራቸው ሥራዎች በግልጥ የሚታወቅ እውነት ስለሆነ ነው። ነጆ የግብርና ኮሌጅ መምህር በነበረበት ጊዜ ዲ/ን ዳንኤል የተረጎመውን የኦሮምኛ ቅዳሴ ትርጉም ከምትኩ ተኮላ ጋር ቀምተው አሳትመው ካሰራጩት በኋላ ዲ/ን ዳንኤል በድርጊታቸው ማዘኑን ስለተረዱ የኦሮሚያ ቤተክህነት እንመሰርታለን ብለው በአዲስ መልክ መንቀሳቀስ በጀመሩ ሰሞን ነጆ ላይ ባካኼዱት ጉባኤ የማስመሰል ሽልማት እንደሰጡት ሀገር ያወቀው ፀሐይ የሞቀው ሀቅ ነው።

ይኼንንም ለማድረግ የደፈሩት ከኛ ወገን መንግስት ተሹሟል፣ጊዜው የኛነው በሚል መንፈስ ነው። እውነትም ጊዜው/ተራው የእነሱ መሆኑን የምዕራብ ወለጋን ሀ/ስብከት መንበረ ጵጵስና በመንግስት ታጣቂ ሓይሎች ታግዘው ከክህነት የተሻሩ የሐሰት ሹመኛ ጳጳስ ተብየዎችን ሰብረው እንዲገቡ በማድረግ አረጋግጠውልናል።
ከውስጥ አዋቂ ምንጮች ለመረዳት እንደቻልነው የሀሳቡ ጠንሳሽ እና ባገኘው ምቹ አጋጣሚ ሁሉ የኦሮሚያ ቤተክህነትን በማቀንቀን የታወቀው ይኼው ግለሰብ እንደሆነ ለማረጋገጥ ተችሏል። ብጹዕ አቡነ ሔኖክ ጵጵስና ተሹመው ወደ ምዕራብ ወለጋ ሲመጡ ይህ ግለሰብ የተቀበላቸው በሃይማኖት አባትነታቸው ሳይሆን በዘር ኦሮሞ መሆናቸውን ታሳቢ አድርጎ ነበር። ብጹዕ አቡነ ሔኖክ ገና ከህጻንነት እድሜያቸው ጀምረው ቤተክርስቲያን ውስጥ ያደጉ፣ንጽህና ቅድስናቸውን ጠብቀው የኖሩ፣ዓለምንና ዓለማዊነትን የተጠየፉ፣ሙሉ ጊዜያቸውን ሰጥተው እግዚአብሔርን ለማገልገል የቆረጡ ካህን እንኳን ዘር ጾታ የለውም ብለው በጽኑ የሚያምኑ አባት እንደሆኑ ተረድተናል።
ሆኖም ግን ይህ የጭቃ ውስጥ እሾህ የሆነው ይህ ግለሰብ ማንነታቸውን በውል ሳይረዳ “ሀገረ ስብከቱ በእቅድ መመራት አለበት” እያለ ስለሚደሰኩር እሳቸውም ሀገረ ስብከቱ እንዲያድግ፣ አሠራሩም እንዲዘምን ካላቸው ጽኑ ፍላጎት የተነሳ ይህንን ግለሰብ አቅርበው ከኤች አይ ቪ መቆጣጠርያ ሥራው በተጨማሪ የሀገረ ስብከቱ አስተዳደር ጉባኤ አባል እንዲሆን አደረጉት። እሳቸው ይህንን ሲያደርጉ በሙያው ቤተክርስቲያንን ያገለግላል በሚል ቅን ሐሳብ እንጂ የተሰጠውን ዕድል እንደመልካም አጋጣሚ ተጠቅሞ ምዕመናንን የሚከፋፍል ሐጢያት በድፍረት ይሠራል ብለው ፈጽሞ አልጠረጠሩም ነበር።
ይህ ከክርስቶስ ፍቅር ይልቅ በዘረኝነት ፍቅር የተለከፈው ግለሰብ ግን የሀ/ስብከቱን ሠራተኞች በገንዘብ በመደለል ከጎኑ ካሰለፈ በኋላ ቤተክርስቲያን የምትበጠበጥበትን ስልት ነድፎ በማሰልጠን አሠማራቸው። በሱ አመለካከት “የኦርቶዶክሳውያን ቁጥር የቀነሰው ቅዳሴ በኦሮምኛ ስላልተቀደሰ ነው።” የሚል ሲሆን ይህንን የተሳሳተ መላምቱን ወደ ሕዝቡ ለማስረጽ ጥናት አጠናኹ በማለት ግኝቱን ለሀገረ ስብከቱ እና ለምዕመናን አቀረበ።
በጊዜው የምዕራብ ወለጋ፣ቄሌም ወለጋ እና የአሶሳ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ሔኖክ ሐሳባቸው ከቅንነት የመነጨ መስሏቸው “እኛ አስበን መሥራት የነበረብንን እናንተ አስባችሁ በመጀመራችኹ እናመሰግናለን በርቱ ቀጥሉበት።” በማለት አባታዊ መመርያ ሰጧቸው። ይህ የልብልብ የሰጠው መሰሪ ግለሰብ የተፈጠረለትን ወርቃማ እድል ለመጠቀም ጊዜ አላባከነም። የቤተክርስቲያንን አውደ ምህረት በመጠቀም ያጠናውን ጥናት በተላላኪዎቹ በእነ ገረመው አፈወርቅ፣ ቄስ በዳሳ ቶላ ወዘተ በመጠቀም “እስከ መቼ ከሰሜን የሚመጡ ካህናት ይመሩናል? ቋንቋችን እስከመቼ ተጨቁኖ ይኖራል?” ማስባል ጀመረ።
የዋኹ ምዕመንም እውነት መስሎት ቃላቸውን በመስማት ቤተክርስቲያንም መበጥበጥ ጀመረች። “አካኼዳችሁ ልክ አይደለም ክርስቶስ የሞተው ያመነበት ሁሉ ይድን ዘንድ ነው።” ብለው የሞገቷቸውን በብሔር ኦሮሞ የሆኑ እውነተኛ አባቶችን ስም የማጥፋት ዘመቻ ከፈቱባቸው፣ ከፍ ሲልም የግምቢ ደብረ ፀሐይ መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ የነበሩትን አባት እስከማስደብደብ ደረሱ። ብጹዕነታቸውም ዓላማቸውን በውል ስለተረዱ ይኼንን ከፋፋይ ሀሳባቸውን እንዲያቆሙ ቢገስጿቸውም፣ “ሕዝቡን ከጎናችን አሰልፈናል ከእንግዲህ የሚያስቆመን ኃይል የለም።” በማለት ብጹእነታቸው ላይ ሕዝቡ እንዲያምጽ ከሀ/ስብከት እስከ ወረዳ ቤተክህነት ቀሰቀሱ።
የዋኹን ምዕመን “በቋንቋህ እንዳትማር፣ ቋንቋህ እንዳያድግ ተቃወሙን” ብለው በሐሰት ስለቀሰቀሱት እውነት መስሎት ተደነጋገረ፤ኦርቶዶክሳውያን የሆኑ የሌላ ብሔር ተወላጅ ካህናት እና ምዕመናን ስጋት ውስጥ ወደቁ። ምዕመናን ከቤተክርስቲያን ራቁ፣አስተዋጽዖቸውን ቀነሱ። ብጹዕ አቡነ ሔኖክም በቃላት የማይገለጽ መከራ ተቀበሉ።
በመጨረሻም ያደራጃቸውን ሴሎች በመጠቀም ብጹዕ አቡነ ሔኖክ ምዕራብ ወለጋ ላይ የጀመሩትን ሐዋርያዊ አገልግሎት፣አስደማሚ የሰብከተ ወንጌል ማስፋፊያ መርሐ ግብራቸውን፣የተጀመሩ የአብነት ትምህርት ቤት ማስፋፊያ ፕሮጄክቶቻቸውን ከግብ ሳያደርሱ ጀሌዎቹን አሳምጾባቸው ያለፈቃዳቸው እንዲዛወሩ እና የምዕራብ ወለጋ ሀ/ስብከት እንዲፈርስ እና ዛሬ ለደረሰበት ምስቅልቅል እንዲደርስ አድርጓል። መለያየትን የሚፈጥር በራሱ ላይ ፈርዶ ሀጢያትን ያደርጋል። ስለጀሌዎቹ ማንነት እንመለስበታለን። ይቆየን።

የሕገወጡ ቡድን ዋናው ዘዋሪ

ኦቦ ጉደታ ገላልቻ ይባላል። የፕራይም ሚዲያ ባለቤት ነው። የኦሮሚያ ክልል ባለሥልጣናት የሚሾሙትና የሚሻሩት በእርሱ ዕውቅናና ፈቃድ ነው። አሁንም እነ አካለ ወልድን የሚዲያ ሽፋን ከመስጠት ጀምሮ ከፍተኛውን ድጋፍ የሚሰጠው ይህ ሰው ነው።

ይህ ሰው የሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም የሰልፍ አስተባባሪ ነበር። በኦሮሚያ ክልል ስውሩ መንግሥት የሚመራው በዚህ አካል ነው።


በሲሞን መንገድ ላይ ተገኙት “አባ” ወ/ኢየሱስ ኢፋ (ፍቅሩ ኢፋ) - ክፍል ሁለት

  እኚህ ሰው የእግዚአብሔርን ጥሪ ተቀብለው መንፈሳዊ ትምህርታቸውን መጀመራቸው አያጠራጥርም። በዚህም የሕይወት ምርጫቸውንም ቅዱስ ጳውሎስ “እንደኔ ብትሆኑ እወዳለኹ” ያለውን ተከትለው በሙሉ ጊዜያቸው እግዚአብሔርን እያመሠ...